የታላቁ ዓባይ ወንዝ መነሻ

0
268

👉በምዕራብ ጎጃም ዞን ሰከላ ወረዳ ከጣና ሐይቅ በስተደቡብ አቅጣጫ 167 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ካለችው ከግሺ ተራራ ስር ያለች የጠበል ምንጭ ናት

👉የአካባቢው ማኅበረሰብ ግሼ ዓባይ ምንጭ ብለው ይጠሯታል፡፡ ምንጯ ኩልል ያለ ውኃ የሚፈስባት እና ዙሪያዋ በቀርቀሃ ተክል የተከበበች ናት

👉የዓባይ መነሻ የሆነችው ምንጭ በአቅራቢዋ የቅዱስ ሚካኤል እና የዘርዓብሩክ አብያተ ክርስቲያናት ይገኛሉ

👉በሃይማኖታዊ ትውፊት የዓባይ መነሻ ከፍተኛ የፈውስ እና መንፈሳዊ ኃይልን ማጎናፀፍ የሚችል ጠበል እንደሆነ ይታመናል

👉ጥር 13 ታላቁ የግዮን በዓል በዓባይ መነሻ በሆነችው ሰከላ – ግሽ ዓባይ በድምቀት ይከበራል

👉ዓባይ የታላቅነት፣ የሥልጣኔ፣ የአንድነት እና የጽናት ምልክት ነው

ምንጭ፡- ቪዚት አማራ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here