እንጅባራ በፈረሶች እና በፈረሰኞች ልትደምቅ ቀናት ብቻ ቀሩ!

0
198

ባሕር ዳር: ጥር 14/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የደጋዋ ንግሥት እንጅባራ ከተማ በጥር ከሚደምቁት የአማራ ክልል ከተሞች አንዷ ናት።

85ኛው አንጋፋው የአገው የፈረሰኞች በዓል እየደረሰ ነው። ፈረሶቻቸውን እንደሰው ልጅ በማዘዝ ተመልካችን “አጀብ” የሚያሰኙ ፈረሰኞች ጥር 23 በእንጅባራ ይከትማሉ። በዚህ ቀን የሚቀር ፈረስ እና ፈረሰኛ የለም።

ዓመታዊ በዓሉ በተለየ ድምቀት ይከበራል። በበዓሉ ላይ ተገኝቶ መታደም ልዩ ሀሴትን ይሰጣል። አሚኮ ዲጅታል ሚዲያ ሁነቶችን በሙሉ በሁሉም የማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችን ለተከታዮቹ ያደርሳል። ቤተሰብ እየኾኑ ይጠብቁን።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here