ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ የሐራጅ ጨረታ ማስታወቂያ

0
145

በሰሜን ጎንደር ዞን በጃናሞራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በሥሩ ለሚገኙው የጃ/ወ/ት/ት/ጽ/ቤት አገልግሎት የማይሰጡ የተለያዩ መጽሐፍቶችን በሐራጅ ጨረታ አውዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ በሙሉ መወዳደር የምትችሉ መሆኑን ጽ/ቤቱ ጥሪውን ያስተላልፍል፡፡ ተጫራቾች ማሟላት ያለባቸው መስፈርቶች፡-

  1. በጨረታው ማንኛውም ግለሰብ መሣተፍ ይችላል፣ እንዲሁም መጽሐፍ ያለበት መ/ብርሃን ከተማ ጃ/ወ/ት/ት ጽ/ቤት ሲሆን ጨረታው አንድ ቀን እስኪቀረው ድረስ መጋዘኑ ክፍት ይሆናል፡፡
  2. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ሰባት በመቶ ከሚሞሉት ጠቅላላ ዋጋ አስበው በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በመሥሪያ ቤቱ ገንዘብ ያዥ በመ/ሂ-1 ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  3. አገልግሎት የማይሰጥ መጽሐፍ ሃራጅ ጨረታ ለአንድ ኪ.ግ መነሻ ዋጋ 7.00 /ሰባት ብር/ ሲሆን ዝርዝር መገለጫ /ስፔስፊኬሽን /ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  4. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 50.00 /ሃምሳ ብር/  በመክፈል  ቢሮ ቁጥር 07 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  5. ጨረታው ከ 16/07/2016 እስከ 30/07/2016 ዓ/ም ድረስ በአየር ላይ ይውላል፡፡
  6. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሀሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋና እና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ቢሮ ቁጥር 10 ጃ/ወ/ገ/ ጽ/ቤት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ቀናት ከ16/07/2016 እስከ 30/07/2016 ዓ.ም ድረስ ማስገባት ይችላሉ፡፡
  7. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም በቀን 01/08/2016 ዓ.ም በእለቱ በ8፡30 ታሽጎ 8፡45 ይከፈታል፡፡
  8. ጨረታውን የምናወዳድረው በጠቅላላ ድምር /በሎት/ ድምር ይሆናል፡፡
  9. ተጫራቾች ከጨረታ ሰነዱ ሥርዝ ድልዝ ሊኖረው አይገባም ካለም ፓራፍ ይደረግበት፡፡
  10. መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  11. አሸናፊ የሆነው ተጫራች  ጊዜው ያለፈበትን መጽሐፍ ርክክብ የሚፈፀመው ያሽነፈበትን ጠቅላላ ብር ከገንዘብ ጽ/ቤት አካውንት ገቢ ሲያደረግ ወይም በተቋሙ መሂ/1 ገቢ ሲያደረግ ጃናሞራ ት/ት ጽ/ቤት  መካነ-ብርሃን ከተማ የሚረከቡ ሲሆን ማንኛውም ወጭ በተጫራች የሚሸፈን ይሆናል፡፡
  12. ተጫራቾች ጨረታው ለተከታታይ 40 ቀናት ፀንቶ ይቆያል፡፡
  13. ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ጃናሞራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 10 በአካል በመገኘት ወይም በስ.ቁ. 058 294 00 23 በመደወል ማግኘት ይቻላል፡፡
የጃናሞራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here