ለሁለተኛ ጊዜ  የጨረታ ማስታወቂያ

0
51

የጨረታ ቁጥር፡ EPSS/NCB/PS/11/2018

የኢትዮጵያ መድሃኒት አቅራቢ አገልግሎት ባሕር ዳር ቅርንጫፍ አንድ ኮስትር ወይም ተመሳሳይ መኪና የመቀመጫ ወንበር ከ22-26 ሰዎችን የመያዝ አቅም ያለው ንፅህናውን የጠበቀ ተሸከርካሪ ባስ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለአንድ አመት ለሰራተኛ መከራየት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ማንኛውም በዘርፉ የተሰማሩና በጨረታዉ መሳተፍ የሚፈልጉ ድርጅት ዝርዝር የጨረታ ሰነዱን ከአገልግሎት መ/ቤታችን ማግኘት ይችላሉ፡፡ ለውድድሩ የሚያስፈልጉ መስፈረቶች

  1. ተጫራቾች የዘመኑን ግብር ከፍለው የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የንግድ ምዝገባ የምሰክር ወረቀት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ እና የቲን ሰርተፊኬት፣ ማስረጃዎች ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
  2. ጨረታው ይህ የጨረታ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ቦርድ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ማለትም ከጥር 1/2018 እስከ ጥር 21/2018 ዓ.ም ለ21 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን በ21 ኛው ቀን ጥር 21/2018 ዓ.ም ከረፋዱ 3፡30 ተዘግቶ በዚሁ ቀን ከረፋዱ 3፡40 ባሕር ዳር ከተማ ጣና ሀይቅ ት/ቤት ፊት ለፊት በሚገኘው መ/ቤት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ የጨረታው መዝጊያና መክፈቻ ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ ጨረታው በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሣሣይ ሰዓት ተዘግቶ ይከፈታል፡፡
  3. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን አገልግሎት መ/ቤታችን በአካል በመቅረብ ብር 300 (ሶስት መቶ ብር) በመክፈል ማግኘት ይችላሉ፡፡
  4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት የሰርቪስ አገልግሎት ጠቅላላ ዋጋ ተቀባይነት ባላቸው የአፈጻጸም ዋስትናዎች (ቢድ ቦንድ) በባንክ በተረጋገጠ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና (Unconditional Bank Guarantee) 2 በመቶ ማስያዝ አለባቸው፡፡
  5. ተጫራቾች የዋጋ ማቅረቢያቸዉን እና የጨረታ ማስከበሪያዉን በተለያየ ፖስታ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ተጫራች ድርጅቶች ለሚያቀርቡት ዋጋ በትክክል ሞልተው በግልጽ ማስቀመጥ አለባቸው፡፡
  6. ይህ ጨረታ በአገልግሎት መ/ቤታችን የግዥ መመሪያ መሰረት ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
  7. የጨረታዉ አሸናፊ አሸናፊነቱ በጽሁፍ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ በ5 ቀናት ዉስጥ የጠቅላላ ዋጋዉን 10 በመቶ የዉል ማስከበሪያ ያለቅድመ ሁኔታ ለገዥ የሚከፈል (Unconditional Bank Guarantee) በማሰራት ዉል የመያዝ ግዴታ ይኖርበታል፡፡
  8. የሰርቪስ አገልግሎት ማቅረቢያ ጊዜ ቢያንስ እስከ አንድ አመት ጨረታው ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ ፀንቶ ይቆያል፡፡
  9. የአገልግሎት መ/ቤታችን የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው ፡፡
  1. ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥራችን 058 226 51 52 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

የኢትዮጵያ መድሃኒት አቅራቢ አገልግሎት

ባሕር ዳር  ቅርንጫፍ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here