በምሥራቅ ጎጃም ዞን በሉማሜ ከተማ አስተዳደር የሉማሜ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽ/ቤት የ5 ዓመት ኦዲት ለማስደረግ በግልጽ ጨረታ በጋዜጣ አወዳድሮ ለማስደረግ ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶችን የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን እየገለጽን፡፡
- በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የዘመኑ ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን/ ያላቸው፡፡
- የቫት ተመዝጋቢየሆኑ፡፡
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ በተ.ቁ 1-4 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸው ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫራቻ ሰነዶች ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፊኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ ብቻ በመክፈል ቢሮ ቁጥር 02 ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ብር ሁለት በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆነ ሁለት ቅጁዎች ዋና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በጽ/ቤቱ በገ/ግ/ፋ/ን/አስ/ደ/የስራ ሂደት ወይም ቢሮ ቁጥር 01 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት ከ08/07/2017 ዓ.ም እስከ 23/07/2017 ዓ.ም እስከ 3፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም በገ/ግ/ፋ/ን/አስ/ደ/የስራ ሂደት ክፍል ቢሮ ቁጥር 02 በቀን 23/07/2017 ዓ.ም በ 3፡00 ታሽጎ በ4፡00 ይከፈታል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 02 ድረስ በአካል መገኘት ወይም በ 058 772 06 45 /06 45 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
- መ/ቤቱ ሃያ አምስት በመቶ የመቀነስ ወይም የመጨመር መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ተጫራቾች ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብር /with hold tax/ ከግዥው ዋጋ ላይ የሚቀነስ ይሆናል፡፡
- አሸናፊው ማሸነፉ ከተነገረበት ቀን ጀምሮ በ5 ቀናት ውስጥ ጽ/ቤት ድረስ በመምጣት ውል መያዝ አለበት፡፡
- አሸናፊው ውል ሲይዝ የውል ማስከበሪያ አስር በመቶ በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይኖርበታል፡፡
- አሸናፊው የሚለየው በሎት ነው፡፡
የሉማሜ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽ/ቤት