በአፈ/ከሣሽ የአገው ግምጃ ቤት ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት እና በአፈ/ተከሣሾች 1ኛ. አቶ ገነቱ ይዘንጋው፣ 2ኛ. አቶ ፈንታሁን አላምረው፣ 3ኛ. ወ/ሮ ብርሃኔ ሞላ መካከል ስላለው የአፈጻፀም ክስ ክርክር ጉዳይ በግምጃ ቤት ከተማ 02 ቀበሌ በአዋሳኝ በምሥራቅ አጥናፍ አለማየሁ፣ በምዕራብ መንገድ፣ በደቡብ ነብዩ ኢሳያስ እንዲሁም በሰሜን መንገድመካከል የሚገኘው የ2ኛ እና የ3ኛአፈ/ተከሳሽ መኖሪያ ቤት መነሻ ዋጋው 407,449.60 (አራት መቶ ሰባት ሺህ አራት መቶ አራባ ዘጠኝ ብር ከስልሳ ሳንቲም) ይሸጣል፡፡ ጨረታውን ከጥር 18/2018 ዓ.ም እስከ የካቲት 18/2018 ዓ.ም በጋዜጣ በማዋል ጨረታው የካቲት 19/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 6፡00 በማጫረት በወቅቱ ጨረታ አሸናፊ ከተገኘም 1/4ኛውን ወዲያውኑ በከፍተኛው ፍርድ ቤት የአማራ ባንክ የሂሳብ ቁጥር 9900017292928 በሆነ ገቢ እንዲያደርግ እና ቀሪውን ደግሞ በቀጠሮው ቀን ይዞ አንዲቀርብ ፍርድ ቤቱ ያስታውቃል፡፡
የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ከፍ/ቤት

