መደበኛ የሊዝ መሬት ጨረታ ማስታወቂያ

0
230

የደጋን ከተማ መሪ ማዘጋጃ ቤት የመሬት ልማት ማኔጅመንት እና ባንክ ቡድን የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ በሚደነግገዉ አዋጅ 721/2004 አንቀፅ 8 ንዑስ አንቀፅ 1 በፊደል ተራ ከ ሀ እስከ ሠ በተዘረዘረዉ መሰረት 02 /ሁለት/ ለድርጅት/ ንግድ 255.6 ካ.ሜ እና 311.42 ካ.ሜ የሚውል ቦታ በግልጽ ጨረታ ለተጫራቾች በጨረታ አወዳድሮ ማስተላለፍ ይፈልጋል፡፡

  1. በመሆኑም መጫረት የሚፈልጉ ማንኛዉም ሰዉ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ከግንቦት 04/09/2017 ዓ/ም ጀምሮ ለ10 ተከታታይ የሥራ ቀናት የቦታዉን ዝርዝር መረጃ እና ለእያዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 500 (አምስት መቶ ብር) ብቻ በመክፈል በደጋን ከተማ መሪ ማዘጋጃ ቤት ቢሮ ቁጥር 2 በሥራ ሰዓት በአካል በመቅረብ መግዛት የሚችሉ መሆኑን እናስታወቃለን፡፡
  2. የጨረታ ሰነድ ማስገቢያ ጊዜ ከግንቦት 04/09/2017 ዓ.ም እስከ ግንቦት 15/09/2017 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ብቻ ይሆናል፡፡
  3. ቦታዉን መጎብኘት ለሚፈልጉ ተጫራቾች በተቋሙ ማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ በሚገለጸዉ መርሀ ግብር መሰረት የምናስጎበኝ ይሆናል፡፡
  4. ጨረታዉ የሚዘጋዉ ግንቦት 15/09/2017 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ይሆናል፡፡
  5. ጨረታዉ የሚከፈተዉ ግንቦት 18/09/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 04፡00 በደጋን ከተማ መሪ ማዘጋጃ ቤት ሁሉም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ይሆናል፡፡
  6. ስለጨረታዉ ዝርዝር መረጃ በጋዜጣ እና በአብክመ ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ዌብ ሳይት እንዲሁም በደጋን ከተማ መሪ ማዘጋጃ ቤት ቢሮ በሥራ ሰዓት በአካል በመቅረብ መረጃ ማግኘት ይቻላል፡፡
  7. ተጫራቾች በሳይት ፕላን ላይ በተገለፀዉ እና በከተማዉ መዋቅራዊ ፕላን መሰረት ደረጃዉን የጠበቀ ግንባታ መስራት ይጠበቅባቸዋል፡፡
  8. መስሪያ ቤቱ ጨረታዉን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡

ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 09 12 47 58 18 /09 31 63 37 72 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

የደጋን ከተማ መሪ ማዘጋጃ ቤት

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here