የአብ ጠቅላላ የኮንስትራክሽን ሥራ እና ግብዓት አቅራቢ ኃ/የተ/የግ/ማህበር በምሥራቅ ጎጃም ዞን ደጀን ዙሪያ ወረዳ ኩራር ቀበሌ ልዩ ቦታ ዥንጎ ተብሎ በሚጠራው ቦታ የጅፕሠም ማዕድን ማምረት ሥራ ፈቃድ እንዲሰጣቸው መሥሪያ ቤታችንን ጠይቀዋል፡፡
የጂኦግራፊክ ኮኦርዲኔቶችም፡-
Adindan UTM Zone 37N
Geographicn Coordinates of the license area
No | Easting | Northing |
7 | 407265 | 1115422 |
8 | 407205 | 1115311 |
9 | 407252 | 1115171 |
10 | 407363 | 1115123 |
11 | 407363 | 1114804 |
No | Easting | Northing |
1 | 407526 | 1114763 |
2 | 407504 | 1114825 |
3 | 407524 | 1115129 |
4 | 407532 | 1115211 |
5 | 407338 | 1115339 |
6 | 407317 | 1115419 |
ብሎክ ቁጥር | በሰሜን | በደቡብ | በምዕራብ | በምሥራቅ |
1 | የግለሰብ ይዞታ | የግለሰብ ይዞታ | የግለሰብ ይዞታ | የግለሰብ ይዞታ |
ስለዚህ የተጠየቀውን ፈቃድ ከመስጠታችን በፊት በተጠቀሰው አካባቢ በተለይም ከዚህ በላይ በተመለከቱት የጂኦግራፊክ ኮኦርዲኔቶች በሚከለል ቦታ ላይ ይገባኛል የሚል ካለ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሰባት /07/ ቀናት ውስጥ ተቃውሞውን በጽሑፍ ለመሥሪያ ቤታችን እንዲያቀርብ እናሳስባለን፡፡ ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 058 222 12 37/21 42 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
የአብክመ ማዕድን ሃብት ልማት ቢሮ