ቢቤት ትሬዲንግ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በምሥራቅ ጎጃም ዞን ፣በደብረኤልያስ ወረዳ፣ ቀበሌ ገነት ፣ልዩ ቦታው በለጠች ወንዝ ፣ ተብሎ በሚጠራው ቦታ የግራናይት ማዕድን ማምረት ሥራ ፈቃድ እንዲሰጣቸው መሥሪያ ቤታችንን ጠይቀዋል፡፡
የጂኦግራፊክ ኮኦርዲኔቶችም፡-
Adindan UTM Zone 37N
Geographic Coordinates of the license area
Points | Easting | Northing |
1 | 312577 | 1123271 |
2 | 312223 | 1122749 |
3 | 312156 | 1122271 |
4 | 312319 | 1122307 |
5 | 312684 | 1123214 |
አዋሳኝ
በሰሜን | በደቡብ | በምዕራብ | በምሥራቅ |
በለጠች ወንዝ | ቱባ ኮመርሻል ምርመራ ቦታ | ባዶ ቦታ | ባዶ ቦታ |
ስለዚህ የተጠየቀውን ፈቃድ ከመስጠታችን በፊት በተጠቀሰው አካባቢ በተለይም ከዚህ በላይ በተመለከቱት የጂኦግራፊክ ኮኦርዲኔቶች በሚከለል ቦታ ላይ ይገባኛል የሚል ካለ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሰባት /07/ ቀናት ውስጥ ተቃውሞውን በጽሑፍ ለመሥሪያ ቤታችን እንዲያቀርብ እናሳስባለን፡፡ ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 058 222 12 37/21 42 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
የአብክመ ማዕድን ሃብት ልማት ቢሮ