አትላስ ኢንተርናሽናል ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር በሰሜን ሸዋ ዞን ባሶናወራና ወረዳ ጉዶበረት ቀበሌ ልዩ ቦታው ታችሙሽ ተብሎ በሚጠራው ቦታ የድንጋይ ከሰል ማዕድን ማምረት ሥራ ፈቃድ እንዲሰጣቸው መሥሪያ ቤታችንን ጠይቀዋል፡፡
የጂኦግራፊክ ኮኦርዲኔቶችም፡-
Adindan UTM Zone 37N
Geographic Coordinates of the license area
Block:-1
id | x | y |
1 | 571444 | 1081267 |
2 | 570716 | 1081155 |
3 | 570852 | 1080949 |
4 | 571274 | 1080807 |
5 | 571912 | 1081260 |
አዋሳኝ ቦታዎች
በሰሜን | በደቡብ | በምዕራብ | በምሥራቅ |
ገብሩ ወንድፈር | ብሉ ናይል | ሀ/ገብርኤል ተስፋየ | አየለ አድማሱ |
ስለዚህ የተጠየቀውን ፈቃድ ከመስጠታችን በፊት በተጠቀሰው አካባቢ በተለይም ከዚህ በላይ በተመለከቱት የጂኦግራፊክ ኮኦርዲኔቶች በሚከለል ቦታ ላይ ይገባኛል የሚል ካለ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሰባት /07/ ቀናት ውስጥ ተቃውሞውን በጽሑፍ ለመሥሪያ ቤታችን እንዲያቀርብ እናሳስባለን፡፡ ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 058 222 12 37/21 42 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
የአብክመ ማዕድን ሃብት ልማት ቢሮ