ሀሴት አነስተኛ ማዕድን ማውጣት ኃ/የተ/የግ/ ማህበር በሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ ቀበሌ እርን ቆላ ቅምበርበሬ (ተከዜ ተፋሰስ) ተብሎ በሚጠራው ቦታ የወርቅ ማዕድን ምርት ማምረት ሥራ ፈቃድ እንዲሰጣቸው መሥሪያ ቤታችንን ጠይቀዋል፡፡
የጂኦግራፊክ ኮኦርዲኔቶችም፡-
Adindan UTM Zone 37N
Geographic Coordinates of the license area
Block:-1
| id | X | Y | 
| 1 | 471140 | 1476911 | 
| 2 | 471311 | 1476924 | 
| 3 | 471313 | 1476801 | 
| 4 | 471171 | 1476782 | 
አዋሳኝ ቦታዎች
| በሰሜን | በደቡብ | በምዕራብ | በምሥራቅ | 
| ተከዜ | እማጎጥ(ተከዜ) | ቅምበርበሬ | ተከዜ | 
ስለዚህ የተጠየቀውን ፈቃድ ከመስጠታችን በፊት በተጠቀሰው አካባቢ በተለይም ከዚህ በላይ በተመለከቱት የጂኦግራፊክ ኮኦርዲኔቶች በሚከለል ቦታ ላይ ይገባኛል የሚል ካለ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሰባት /07/ ቀናት ውስጥ ተቃውሞውን በጽሑፍ ለመሥሪያ ቤታችን እንዲያቀርብ እናሳስባለን፡፡ ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 058 222 12 37/21 42 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
የአብክመ ማዕድን ሃብት ልማት ቢሮ

