ሾተላዩ ፖለቲካ እና የድርድሮች ምክነት

0
199

በአማራ ክልል የተፈጠረው
በትጥቅ የታገዘ ግጭት እልባት
እንዲሰጠው ብዙዎች እየጠየቁ
ነው። ሰላም እንዲሆን ሁሉም
ይፈልጋል። ነገር ግን ሰላም
የሚመጣበት መንገድ ላይ
ተመሳሳይ አቋም ያለ
አይመስልም።
በአዲስአበባ ዮኒቨርሲቲ
የፖለቲካ ሳይንስ መምህር የሆኑት
ዶክተር ዳር እስከዳር ታዬ
ለበኩር እንደተናገሩት የሰላም
ድርድር ወይም ንግግር ሁሉንም
ለአሸናፊነት የሚያበቃ ሀይል
ነው። ግጭቶችን ለማርገብ፣
ቀውሱን ለመቀልበስ እና ወደ
ሰላማዊ ሁኔታ ለመመለስ
ሀቀኛ ንግግሮች ገቢራዊ ሊሆኑ
እንደሚገባ የጠቆሙት ምሁሩ
በሰጥቶ መቀበል መርህ ጫፍ
ላይ ሳይሆኑ ወደ መሃሉ
በመቅረብ ለሰላም መሥራት
እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል የተለያዩ
የፖለቲካ ፓርቲዎች ንግግር
እንዲደረግ የመሣሪያ አፈሙዞች
እንዲስተካከሉ እየወተወቱ
ይገኛሉ። ለፖለቲካዊ ችግሮች
ፖለቲካዊ ምላሽ ማዘጋጀት
እንጅ ውጊያን አማራጭ ማድረግ
አውዳሚ መሆኑን ከታሪክ
ሳይሆን አሁን እየሆነ ካለው
መማር ይቻላል።

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here