በአፍሪካ ቀዳሚዎቹ አሥር  ግድቦች

0
15

በአፍሪካ በውኃ ግፊት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ከኃይል ማግኛ አማራጮች ተመራጩ እና ቀዳሚው ነው:: አንዳንድ ሀገራት ደግሞ ከቅሪት አካል ከሚገኝ ነዳጅ እና ከፀሐይ እና ከእንፋሎት በሚገኝ ኃይል ላይ እንደተመረኮዙ ናቸው::

ሀገራት ከብክለት ነፃ በሆነ የኃይል አማራጭ ላይ መመስረት እንደሚኖርባቸው ታምኖበት በዓለም አቀፍ ደረጃ ግብ ተጥሎ በመንቀሳቀስ ላይ ናቸው ፤ብክለትን ዜሮ ለማድረስ::

በአህጉራችን አፍሪካ በውኃ ግፊት  የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት ቀዳሚዎቹን አሥር ግድቦች እንመልከት፤

10 . መገኛ ሀገር – ናይጀሪያ

የግድቡ መጠሪያ – ካይንጂ ግድብ

የሚያመነጨው የኃይል መጠን- 760 ሜጋዋት

ግድቡ በሚያመነጨው የኤሌክትሪክ ኃይል ገጠሩን በማዳረስ የኢንዱስትሪ እድገትን ያመጣል በሚል ታመኖበት ነበር የተሠራው:: ይሁን እንጂ፣ “በተርባይን” ወይም በመቅዘፊያ ችግር፣ በጥገና እጦት እና በደለል መሞላት ከአቅም በታች አገልግሎት እየሰጠ ነው::

  1. መገኛ ሀገር – ጋና

የግድቡ መጠሪያ – አኮሶምቦ ግድብ

የሚያመነጨው የኃይል መጠን -1020 ሜጋዋት

የጋናው ኦኮሶምቦ ግድብ በቮልታ ወንዝ ላይ በ1965 ተገንብቶ የተጠናቀቀ ነው:: ግድቡ በዓለማችን ትልቁን ሰው ሠራሽ ሐይቅ የቮልታ ሐይቅን አስገኝቷል::

ከግድቡ የሚገኘው የኤሌክትሪክ ኃይል ለሀገር ውስጥ እንዱስትሪዎች የብረት ፋብሪካን ለመሳሰሉት የኃይል ምንጭ  ሆኗል:: በመጀመሪያዎቹ ዓመታት ለቤኒን እና ቶጐ ጐረቤት ሀገራትም አገልግሏል::

  1. መገኛ ሀገር ኢትዮጵያ

የግድቡ መጠሪያ – ተከዜ ግድብ

የሚያመነጨው የኃይል መጠን – 1 ሺህ 200 ሜጋ ዋት

በ2009 እ.አ.አ በተከዜ ወንዝ ላይ የተገነባ ባለ ድርብ ቅስት ግድብ ነው::

ግድቡ ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ሰሜናዊ ቀጣና በተነሳው ግጭት ፈተና ቢገጥመውም የኢትዮጵያን የልማት እቅድ በመደገፍ ላይ ይገኛል::

  1. መገኛ ሀገር – ሱዳን

የግድቡ መጠሪያ – ሜሮዌ ግድብ

የሚያመነጨው የኃይል መጠን – 1 ሺህ 250 ሜጋዋት

በሀገሪቱ ትልቁ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ ነው፤ በዓባይ ወንዝ ላይ ነው የተሠራው::

በ2009 እ.አ.አ ሥራው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል:: ለሀገሪቱ ብሔራዊ የኃይል ቋት ከፍተኛ መጠንም ያበረክታል:: በወንዙ ዳር ላሉ ከተሞች የኤሌክትሪክ ኃይል አመንጭቶ ከግድቡ በሚለቀቅ ውኃ ለመስኖ ልማት ውሏል::

ግድቡ ለኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫነት የተገነባው ሀገሪቱ ከቅሪት አካል ነዳጅ ያላትን ጥገኝነት ለመቀነስ መሆኑም ተጠቅሷል::

  1. መገኛ ሀገር – ዛምቢያ፣ ዚምባቡዌ

የግድቡ መጠሪያ – ካሪባ ግድብ

የሚያመነጨው የኃይል መጠን – 1 ሺህ 626 ሜጋዋት

በዛምቢያ እና ዚምባቡዌ  መካከል ባለው የዛምቤዚ ወንዝ ላይ የተገነባ ድንበር ተሻጋሪ ትብብርን የሚያሳይ ነው፤ ካሪባ ግድብ:: ለሁለት ሀገራት የኃይል ምንጭ ሆኖም ያገለግላል::

ለዚምባቡዌም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በመሰረተ ልማት ማከፋፈያ እና የውኃ መጠን መቀነስ ቢገጥማትም ወሳኝ ዓቅም ሆኖ ቀጥሏል::

  1. መገኛ ሀገር- ኮንጐ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ

የግድቡ  መጠሪያ- የኢንጋ ግድቦች

የሚያመነጩት የኃይል መጠን- 1 ሺህ 775 ሜጋዋት

የኢንጋ ግድቦች በኮንጐ ወንዝ ላይ የሚገኙ ሁለት ትልልቅ ግድቦችን ያካተተ ነው::

ተስፋ ሰጪ  የኢሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ ተብሎም ነው የሚታሰበው:: በግድቡ ላይ ሌላ ሦስተኛ “ግራንድ ኢንጋ” የተሰኘ ግድብ ለመገንባት ውይይቶች ሲካሄዱ ቆይተዋል፤ በፖለቲካ አለመረጋጋት እና በገንዘብ እጥረት እውን ሳይሆን ቢቀርም::

  1. መገኛ ሀገር- ኢትዮጵያ

የግድቡ መጠሪያ – ግልገል ጊቤ ሦስት ግድብ

የሚያመነጨው የኃይል መጠን -1 ሺህ 870 ሜጋዋት

ግድቡ በኢትዮጵያ በትልቅነቱ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል::   በኦሞ ወንዝ ላይ በ2016 እ.አ.አ ተገንብቶ የተጠናቀቀ ነው:: የግድቡ ግንባታ ሀገሪቱ በአፍሪካ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ባለቤት ለመሆን ያላትን ቁርጠኝነት ማሳያ መሆኑን ልብ ይሏል::

  1. መገኛ ሀገር – ሞዛምቢክ

የግድቡ መጠሪያ – ካሆራ ባሳግድብ

የሚያመነጨው የኃይል መጠን -2 ሺህ 070 ሜጋዋት

ከደቡባዊ አፍሪካ ሀገራት ቀደም ብሎ  በዛምቤዚ ወንዝ ላይ የተገነባ ግድብ ነው:: ሞዛምቢክ ከግድቡ የሚመነጨውን የኤሌክትሪክ ኃይል ለደቡብ አፍሪካ በመሸጥም የምጣኔ ሀብቷን ትደጉማለች::

  1. መገኛ ሀገር – ግብፅ

የግድቡ መጠሪያ – አስዋን ግድብ

የሚያመነጨው የኃይል መጠን- 2 ሺህ 100 ሜጋ ዋት

የአስዋን ግድብ በ1970 እ.አ.አ ነው ግንባታው የተጠናቀቀው:: ግድቡ ከኃይል ማመንጫነት ባለፈ አገሪቱ በመስኖ የእርሻ መሬቷን እንድታለማ አስችሏታል:: ግድቡ  በዓለም ላይ ካሉት ትልልቅ የውኃ ማጠራቀሚያዎች አንዱ ለመሆን በቅቷል፤ የናስር ሐይቅን ፈጥሮ:: ግድቡ የሀገሪቱ የጥንካሬ ተምሳሌት ነው::

  1. መገኛ ሀገር ኢትዮጵያ

የግድቡ መጠሪያ – ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ

የሚያመነጨው የኃይል መጠን –  6 ሺህ 450 ሜጋ ዋት

በዓባይ ወንዝ ላይ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በ2011 እ.አ.አ ግንባታው ተጀምሮ በ2025 እ.አ.አ  የጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል:: ኢትዮጵያ  ግንባታውን አጠናቃ ኃይል መስጠት ሲጀምር ለሀገር ውስጥ፣ ጐረቤት ሀገራትን እና ሰሜን አፍሪካን በማድረስ ቀዳሚ የኤሌክትሪክ ኃይል ባለቤት  ያደርጋታል::

ምንጭ፡- አፍሪካን ኤክስፓነንት ድረገጽ

(ታምራት ሲሳይ)

በኲር የጳጉሜን 3 ቀን 2017 ዓ.ም ዕትም

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here