በድጋሚ የወጣ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
20

የአብክመ ጤና ቢሮ የሚጠቀምባቸውን የስራ ክፍሎች አመታዊ ውል በመያዝ ለማፀዳት በዘርፉ ለተሰማሩ አውት ሶርስ በማድረግ አገልግሎቱን ማግኘት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ መወዳደር ይችላሉ፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን ሰርተፍኬት/ የሚያቀርቡ፡፡
  3. ከላይ በተራ. ቁጥር 1-2 የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸዉ ጋር አያይዘዉ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. የሚገዛው ዕቃ ጠቅላላ ዋጋ ከ200,000.00 /ሁለት መቶ ሽህ ብር/ በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ የቫት ሰርተፍኬት ኮፒ ማስያዝ አለበት፡፡
  5. የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ ለሚወዳደሩት ጠቅላላ ዋጋ 2በመቶ በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና የሚያስይዙ ፡፡
  6. ማንኛውም ተጫራች የመወዳደሪያ ሃሳቡን በታሸገ ፖስታ በጤና ቢሮ በግዥ ፋይ/ ንብ/ አስ/ ዳይሬክቶሬት ግዥ ክፍል በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  7. ጨረታዉ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት በ16ኛው ቀን 8:30 ታሽጎ 9፡00 ይከፈታል፡፡ ሆኖም ዕለቱ የስራ ቀን ካልሆነ በተከታዩ የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት የሚታሸግና የሚከፈት ይሆናል፡፡
  8. ሌሎች ተጫራቾች በሚያቀርቡት ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይቻልም፡፡
  9. ቢሮው የግዥውን መጠን እስከ 20በመቶ ሊጨምር ወይም ሊቀንስ ይችላል፡፡
  10. የጨረታዉ አሸናፊ የሆነ ድርጅት ያሸነፈውን የፅዳት ቁሳቁስ እና የቢሮ ፅዳት አገልግሎት በጨረታ ሰነዱ ላይ በተቀመጠው አግባብ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡
  11. በጨረታው ለመወዳደር የሚፈልግ ተጫራች የመጫረቻ ሰነዱን ጨረታው ከወጣበት ከነሐሴ 26/2017 ዓ.ም ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት እስከ 11፡30 ድረስ የማይመለስ ብር 500.00 /አምስት መቶ ብር/ በመክፈል ከቢሮው የሰነድ ሽያጭ ክፍል መውሰድ ይችላል ፡፡
  12. ቢሮው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  13. ስለ ጨረታዉ መረጃ ከፈለጉ አብክመ ጤና ቢሮ ስልክ ቁጥር 058-222-11 27 በመደወል ተጨማሪ መረጃ ማግኘት ይቻላል፡፡

የአብክመ ጤና ቢሮ

 

 

 

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here