በድጋሚ የወጣ ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

0
75

የጎንደር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለማኒፋክቸሪንግ ፣ለኤሌክትሪክሲቲ እና ለኮንስትራክሽን የግንባታ ጥሬ እቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል ፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይጋብዛል።

  1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
  3. የግዥዉ መጠን ብር 100,000/ መቶ ሽህ ብር/ እና በላይ የሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸዉን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ
  4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተ.ቁ 1-3የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  5. የሚገዙ ዕቃዎችን መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
  6. የጨረታው ዉድድር በነጠላ ድምር ዋጋ ሆኖ አሸናፊ እና ተጫራቾች ያሸነፉትን እቃዎ በራሱ ወጭ በማጓጓዝ በባለሙያዎች እየተረጋገጠ ዕቃዎችን ገቢ ይደረጋል፡፡
  7. የጨረታ ተወዳዳሪዎች በሌሎች ተወዳዳሪዎች ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ የለባቸውም፡፡
  8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት ብር 10,000/አስር ሽህ ብር / በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሰ.ፒ.ኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸዉ፡፡
  9. ማንኛውም ተጫራቾች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ማለትም ዋናና ቅጅ በእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ ወይም ገጽ ላይ የድርጅቶች ማህተም በማስቀመጥ በጥንቃቄ  በታሸገ ፖስታ በጎንደር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በግዥና ፋ/ን/አስ/ ቡድን በተዘጋጀው  የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰአት እንዲሁም ቅዳሜ እና እሁድን  ጨምሮ ከ2፡30 እስከ 11፡00 ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  • የጨረታው ማስታወቂያ ከወጣበት ከ 6 /08/2017 ዓ.ም እስከ 20/08/2017ዓ.ም ዘወትር በስራ ሰዓት ከጥዋቱ 2፡30-11፡00 እንዲሁም በ21/08/2017 ዓ.ም እሰከ ጥዋቱ 3፡00 ስዓት ድረስ ማስገባት ይችላሉ፡፡
  • ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥና ፋ/ን/አስ/ ቡድን ክፍል 21/08/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡05 ታሽጎ በ4፡00 ሰዓት ይከፈታል፡፡
  • የጨረታ ሰነድ መሸጫ ብር 150 /አንድ መቶ ሃምሳ ብር/ ሲሆን ስለ ጨረታ ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ግዥና ፋ/ን/አስ/ቡድን ድረስ በአካል በመገኘት ወይም ቁጥር 0581118360 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡

የጎንደር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here