በድጋሜ የወጣ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
40

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የማዕከላዊ አርማጭሆ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ለ2018 በጀት ዓመት በወረዳዉ ላሉ ተሽከርካሪዎች አገልግሎት የሚዉሉ የመኪና መለዋወጫ እቃ አቅርቦቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸዉ፡፡
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸዉ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
  4. የግዥዉ መጠን ብር 200,000 /ሁለት መቶ ሽህ ብር/ እና ከዚያ በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  5. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-4 የተጠተሱትንና የሚመለከታቸዉን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸዉ ጋር አያይዘዉ ማቅረብ አለባቸዉ፡፡
  6. የሚገዙ እቃዎችን አይነት እና ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ከማዕ/አ/ወ/ገንዘብ/ጽ/ቤት ከዋና ገንዘብ ያዥ ቢሮ ቁጥር 05 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት ብር የዕቃዉን ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ በመሂ 1 በመክፈል ማቅረብ አለባቸዉ፡፡
  9. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን አንድ ወጥ በሆነና ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋናና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በመ/ቤታችን ቢሮ ቁጥር 4 በተዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት እስከ ህዳር 30/2018 ዓ.ም 3፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  10. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ህዳር 30/2018 ቢሮ ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ላይ ታሽጎ 3፡05 ይከፈታል፡፡
  11. መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  12. ስለጨረታዉ ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ድረስ በአካል በመገኘት መጠየቅ ይችላሉ፡፡
  13. የጨረታ መክፈቻው ቅዳሜና እሁድ ወይም በአል ከሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን እና በተመሳሳይ ለዓት የሚከፈት ይሆናል፡፡

የማዕከላዊ አርማጭሆ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here