በድጋሜ የወጣ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
109

በአብክመ  የርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት   ሎት 1 የጽህፈት መሳሪያዎች   ግዥ፣ ሎት 2 የጽዳት እቃዎች እና  ሎት 3 ኤሌክትሮኒክስ እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ የአገልግሎት ግዥ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾችን ይጋብዛል፡፡

  1. በዘርፉ በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ሥራ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
  3. የግዥው መጠን 200,000.00 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) በላይ ከሆኑ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር ከ1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 200.00 (ሁለት መቶ ብር) ከግዥ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 33 በመክፈል የጨረታ ሰነዱን   ማግኘት ይችላሉ፡፡
  6. ሎት 3 የኤልክትሮኒክስ እቃዎች ቴክኒካልና ፋይናሻል ለየብቻዉ በታሸገ ፖስታ መሆን አለበት፡፡
  7. ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት ግዥ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ሁለት በመቶ (ቢድ ቦንድ) በጨረታ ሠነዱ የተገለፀውን የብር መጠን በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና (Unconditional Bank Guarantee) ወይም በጥሬ ገንዘብ ከሆነ በአብክመ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤ በተሰጠ ሕጋዊ ደረሰኝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  8. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ መሆን አለበት፡፡ ጨረታዉም በርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ግዥ፣ ፋይናንስ እና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክተር የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 30 በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ጨረታው በጋዜጣ በግልጽ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  9. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥ፣ ፋይ/ንብ/ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 30 በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ታሽጐ በዚያዉ ቀን 4፡00 ላይ ይከፈታል፡፡ ይሁን እንጂ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙም ጽ/ቤቱ ጨረታውን የመክፈት መብት አለው፡፡
  10. ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
  11. ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 30 በአካል በመገኘት ወይም በፋክስ ቁጥር 058 220 1068 በመላክ ወይም በስልክ ቁጥር 058 220 2030 ወይም 058 220 1081 በመደወል መረጃ ማግኘት ይቻላል፡፡

አብክመ ርዕሰ መስተዳድር /ቤት

ባህር ዳር

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here