ኢትዮጵያ በፖስታ ማህበር

0
212

ዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ የኢትዮጵያን የፖስታ አገልግሎት ለማቋቋም በማሰባቸው የዓለም ፖስታ ማህበር አባል ለመሆን ለስዊዝ ፕሬዚደንት በድጋሜ ደብዳቤ የላኩት በያዝነው ሳምንት መጋቢት 10 ቀን 1887 ዓ.ም ነበር።

ንጉሡ ከዚህ በፊት የካቲት 10 ቀን 1885 ዓ.ም ላይ በላኩት ደብዳቤ የጠየቁ ቢሆንም የተሰጣቸው ምላሽ በቅድሚያ የፖስታ ስራ ማካሄዱን እንዲጀምሩ የሚል ነበር። በመሆኑም በ1886 ዓ.ም በፓሪስ ውስጥ በምስላቸው የተቀረፀ ቴምብር በስራ ላይ አዋሉ። ይህን ካደረጉ በኋላ ነበር በድጋሜ የፃፉት፣ ከዛሬ 129 አመታት በፊት በፊት መሆኑ ነው።

ምንጭ፤ ጳውሎስ ኞኞ

(መሰረት ቸኮል)

በኲር መጋቢት 9 ቀን 2016 ዓ.ም ዕትም

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here