ጣና ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አ.ማ ስማቸው ከዚህ በታች የተጠቀሰው ተበዳሪ ያለባቸውን ብድር በወቅቱ ባለመክፈላቸው ምክንያት ተቋሙ በአነስተኛ የፋይናንስ ስራ አዋጅ ቁጥር 626/2001 እና አዋጅ ቁጥር 97/90 በተሠጠው ስልጣን መሠረት ብድሩን በዋስትና ወይም በመያዣነት የተያዘውን የመኖሪያ ቤት በሐራጅ ጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
የቅርንጫፍ ስም | የተበዳሪ ስም | የንብረት አስያዥ ስም | የንብረቱ አይነት | የቤቱ ስፋት | የሃራጅ መነሻ ዋጋ | ሃራጅ የሚካሄድበት ቦታ |
ዱርቤቴ ቅርንጫፍ | አቶ ሃብታሙ አስማረ ደበበ እና አቶ ዘለቀ ደስታ አሻግሬ | አቶ ሃብታሙ አስማረ ደበበ | የድርጅት ቤትና ቦታ | 500 ካ.ሜ | 1,647,142.89 | ጣና ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም በዱር ቤቴ ቅርንጫፍ ሃምሌ 2/2017 ዓ/ም ከጠዋቱ 5፡00 |
ዱርቤቴ ቅርንጫፍ | አቶ እያዩ አድጎ መኮነን እና አቶ ብጹእአምላክ አስፋ አያሌው | አቶ እያዩ አድጎ መኮነን | የመኖሪያ ቤትና ቦታ | 200 ካ.ሜ | 739,112.4 | ጣና ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም በዱርቤቴ ቅርንጫፍ ሃምሌ 2/2017 ዓ/ም ከጠዋቱ 5፡00 |
ማሳሰሰቢያ፡-
- ማንኛውም ተጫራች ወይም ህጋዊ ወኪል የሐራጁን 5 በመቶ መነሻ ዋጋ መጫረት ይቻላል፡፡
- አሸናፊው ጨረታውን ካሸነፈበት ቀን ጀምሮ ገንዘቡን በ15 ቀናት ውስጥ አጠቃሎ መክፈል ያለበት ሲሆን ይህን ካላደረገ ለሐራጅ መነሻ ያስያዘው ገንዘብ ተመላሽ ሳይሆን ውሉ ይቋረጣል፡፡
- ሐራጁ የሚካሄድበት በአማራ ክልል ሰሜን ጎጃም ዞን ዱርቤቴ ከተማ 01 ቀበሌ ዱርቤቴ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ነው፡፡
- በጨረታው ላይ ተጫራቾችና ባለንብረቶች ወይም ህጋዊ ወኪሎችቻቸው መገኘት አለባቸው፡፡
- ተቋሙ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- በመንግስት የሚፈለጉ ግብሮችን እና የስም ማዛወሪያዎችን እና ሌሎች ወጭዎችን የጨረታው አሸናፊ ይሸፍናል፡፡
- ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር +251-582-230-783 ደውለው መጠየቅ ይቻላል፡፡
ጣና ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አ.ማ