የሊዝ መሬት የጨረታ ማስታወቂያ

0
126
  1. የገርባ ከተማ መሪ ማዘጋጃ ቤት የከተማ መሬት ባንክና ፋይናንሲንግ ልማት ቡድን የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ በሚደነግገው አዋጅ 721/2004 አንቀጽ 8 ንዑስ አንቀጽ 1 በፊደል ተራ ከሀ እስከ ሠ በተዘረዘረው መሰረት ለመኖሪያ አገልግሎት የሚውል 200 ካሬ ሜትር ቦታን በግልጽ ጨረታ ለተጫራቾች ማስተላለፍ ይፈልጋል፡፡
  2. በመሆኑም መጫረት የሚፈልጉ ማንኛውም ሰው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ከ12/09/2016 ዓ/ም ጀምሮ ለ10 ተከታታይ የሥራ ቀናት የቦታውን ዝርዝር መረጃ እና የጨረታ ሰነድ የማይመለስ 300.00 /ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል በገርባ ከተማ መሪ ማ/ቤት ቢሮ ቁጥር 3 በሥራ ሰዓት በአካል በመቅረብ መግዛት የሚችሉ፡፡
  3. የጨረታ ሰነድ ማስገቢያ ጊዜ ከ12/09/2016 ዓ/ም እስከ 23/09/2016 ዓ/ም ከቀኑ 11፡00 ይሆናል፡፡
  4. ጨረታው የሚዘጋው በ23/09/2016 ዓ/ም በ11፡00 ይሆናል፡፡
  5. ቦታውን መጎብኘት ለሚፈልጉ ተጫራቾች በተቋሙ ማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ በሚገለፀው መርሀ ግብር መሠረት የምናስጎበኝ ይሆናል፡፡
  6. ጨረታው የሚከፈተው በ26/09/2016 ዓ/ም ከጠዋቱ በ4፡00 በገርባ ከተማ መሪ ማ/ቤት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይሆናል፡፡
  7. ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ በጋዜጣ እንዲሁም በገርባ ከተማ መሪ ማ/ቤት ዘወትር በሥራ ሰዓት በአካል በመቅረብ ማግኘት ይቻላል፡፡
  8. ተጫራቾች በሣይት ፕላን በተገለፀው እና በከተማው መዋቅራዊ ፕላን መሰረት ደረጃውን የጠበቀ ግንባታ መገንባት ይጠበቅባቸዋል፡፡
  9. መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  10. ለተጨማሪ መረጃ 0920780008፣ 0906416921፣ 0912967158 ወይም 0334540304 በመደወል መጠየቅ ይቻላል፡፡

የገርባ ከተማ መሪ ማዘጋጃ ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here