የሊዝ ጨረታ ማስታወቂያ፤

0
74

የወረታ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት የከተማ ቦታ ስለመያዝ በደነገገው አዋጅ 72/2004 መሠረት በ2017 በጀት ዓመት ለሁለተኛ ዙር ከ1-5 የተዘረዘሩትን የመሬት ሊዝ ጨረታ ማስተላለፍ ይፈልጋል፡፡

  1. ቀበሌ 04 በአዋሳኝ በምሥራቅ ሸህ ሰኢድ አበበ፣ በምዕራብ መንገድ፣ በሰሜን ፍቃዴ እንዲሁም በደቡብ ትሁኔ መካከል የሚገኝ ቦታ ስፋቱ 400 ካ/ሜትር
  2. ቀበሌ 04 በአዋሳኝ በምሥራቅ እነ እስከዳር ታደሰ ፣በምዕራብ መንገድ፣ በሰሜን ዝቤ እንዲሁም በደቡብ ምስጋና መካከል የሚገኝ ስፋቱ 300 ካ/ሜትር፣
  3. ቀበሌ 01 በአዋሳኝ በምሥራቅ መንገድ ፣በምዕራብ ንጉስ አግማስ፣ በሰሜን አዱኛ አንዲሁም በደቡብ ክፍት ቦታ መካከል የሚገኝ ስፋቱ 500 ካ/ሜትር፣
  4. ቀበሌ 04 በአዋሳኝ በምሥራቅ ቢላል መኮነን ፣በምዕራብ አሊድ ኑርልኝ፣ በሰሜን መንገድ እንዲሁም በደቡብ ቢያድግ መካከል የሚገኝ ስፋቱ 224 ካ/ሜትር፣
  5. ቀበሌ 04 በአዋሳኝ በምሥራቅ መንገድ ፣በምዕራብ ቀበሌ ቤት ፣በሰሜን ግዛቸው እንዲሁም በደቡብ የልፍኝ መካከል የሚገኝ ስፋቱ 108 ካ/ሜትር፣
  6. የጨረታ ሰነድ ቢሮ ቁጥር 17 በመምጣት የማይመለስ 300 /ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል መግዛት ይቻላል፡፡
  7. የጨረታ አይነት መደበኛ፣
  8. የጨረታ ሰነድ የመግዣ ቀን ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀን ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 11፡30 ብቻ ይሆናል፡፡
  9. የጨረታ ሰነድ መሸጫ ጊዜ የሚያልቀው በ10ኛው ቀን 11፡30 ነው፡፡
  10. ጨረታው የሚከፈተው በ11ኛው ቀን ወረታ ከተማ አስተዳደር ከተማ መሰረተ ልማት ጽ/ቤት ከጠዋቱ 4፡00 ታሽጎ 4፡30 ሁሉም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም ጨረታው ይከፈታል፡፡
  11. መሥሪያ ቤቱ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  12. የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ወይም ሲፒኦ በባንክ የተረጋገጠ የገንዘብ ክፍያ ትዕዛዝ ለሚወዳደሩበት አምስት በመቶ ዋስትና ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ አሸናፊው ከተለየ በኋላ ያስያዙት ሲፒኦ የሚመለስ ይሆናል፡፡
  13. የግንባታ ደረጃ ለድርጅት እና ቅይጥ ቤት፡፡
  14. የቦታው አገልግሎት በእያንዳንዱ ምድብ ከሰነዱ ጋር በሚሸጠው ሰነድ ሰንጠረዥ ላይ የተቀመጠው ይሆናል፡፡
  15. ከላይ በአዋሳኝ የተጠቀሱትን ቦታዎች የሚያሸንፉ ተጫራቾች አርባ በመቶ ቅድሚያ ክፍያ መክፈል ይኖርባቸዋል፡፡
  16. ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 058 446 00 26 ደውለው ማግኝት ይችላለሁ፡፡

የወረታ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here