የሊዝ ጨረታ ማስታወቂያ

0
42

የጨረታ ዙር የ2018 በጀት ዓመት 1ኛ ዙር ጨረታ

የጨረታዉ ዓይነት መደበኛ ጨረታ

  1. የእንጅባራ ከተማ አስተዳደር /ከ/ል/ቤ/ኮ/አገ/ጽ/ቤት የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ በሚደነግገዉ አዋጅ 721/2004 አንቀፅ 8 ንዑስ አንቀፅ 1 በፊደል ተራ ከሀ እስከ ሠ በተዘረዘረዉ መሰረት ለመኖሪያ 12 ( አስራ ሁለት)  እና ለድርጅት7  የተዘጋጁ ቦታዎችን በመደበኛ ጨረታ ለተጫራቾች ማስተላለፍ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም መጫረት የምትፈልጉ እድሜያቸው 18 እና ከዚያ በላይ የሆኑ የጨረታ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከታተመበት  ከመስከረም 19/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 10 /የስራ ቀናት/ ውስጥ የቦታዉን ዝርዝር መረጃ እና የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ለመኖሪያ 300 /ሶስት መቶ/ ብር፣ ለድርጅት 500 /አምስት መቶ/ ብር በመክፈል በእንጅባራ /ከ/አስ/ከ/መ/ል/ጽ/ቤት  ከ/መ/ል/ባ/ ቡድን ቢሮ ቁጥር 004 ዘወትር በስራ ቀን እስከ 11፡00 መግዛት የምትችሉ መሆኑን እናስታወቃለን፡፡
  2. የጨረታ ሰነድ ማስገቢያ ጊዜ ሰነዱን ከገዙበት ቀን ጀምሮ እስከ ሚዘጋበት ቀን ድረስ ዘወትር በስራ ሰዓት ከቀኑ እስከ 11፡00 ብቻ ይሆናል፡፡
  3. ጨረታዉ የሚዘጋዉ ሰነድ ሽያጭ ባለቀበት ቀን ከቀኑ 11፡00 ይሆናል፡፡
  4. ለጨረታ የቀረቡ ቦታዎችን ማስታወቂያው በጋዜጣ ከታተመ በኋላ ከተቋሙ የማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ በሚወጣው ፕሮግራም መሰረት ከባለሙያ ጋር መጐብኘት ይቻላል፡፡
  5. ጨረታው የሚከፈተው ከታሸገበት በቀጣዩ ቀን ከጥዋቱ 3፡00 የመኖሪያ በቀጠዩ ቀን የድርጅት ደግሞ በእንጅባራ ከ/አስተዳደር አዳራሽ ይከፈታል፡፡
  6. የጨረታዉን ዝርዝር መረጃ ከተቋሙ የማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ ማግኘት ይቻላል፡፡
  7. መስሪያ ቤቱ ጨረታዉን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
  8. ማንኛውንም መረጃ ከፈለጉ ስልክ ቁጥር፡ (251) 058 227  00  05 መደወል ይችላሉ፡፡

የእንጅባራ ከተማ አስተዳድር ከ/መ/ል/ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here