በአፈ/ከሣሽ ዳግማዊ አንተነህ እና በተከሣሽ እነ አስናቀች አባተ መካከል ስላለው የአፈፃፀም ክስ ክርክር ጉዳይ በጣና ክ/ከተማ በአቶ አባተ ይመር እና በእ/ይ አማለድ ተገኘ ስም ተመዝግቦ የሚገኝ በምስራቅ ኮብል መንገድ፣ በምዕራብ የአቶ እንደሻው ቤትና ቦታ፣ በሰሜን የአቶ ተገኝ ቤትና ቦታ እንዲሁም በደቡብ ሲሳይ ይትጉ ቤትና ቦታ መካከል ተዋስኖ የሚገኘው ፤ 450 ካ.ሜ የሆነ፤ በመነሻ ዋጋ 5‚028‚226 (አምስት ሚሊዩን ሀያ ስምንት ሽህ ሁለት መቶ ሀያ ስድስት ብር ሆኖ ጥር 2/2018 ዓ/ም ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 6፡00 ድረስ ቤቱ በሚገኝበት ግቢ በግልጽ ጨረታ ይሸጣል፡፡ መጫረት የምትፈልጉ ሁሉ ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ በመያዝ በሰዓቱና በቦታው በመገኘት ተመዝግባችሁ መጫረት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን የመጨረሻ አሸናፊው ያሸነፈበትን ¼ኛውን በሞዴል 85 ማስያዝ የሚጠበቅበት መሆኑን ፍ/ቤቱ ያሣውቃል፡፡
የባሕር ዳርና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍ/ቤት

