የሐራጅ ጨረታ ማስታወቂያ

0
7

በአፈ/ከሳሽ ከፍያለው አያሌው እና በአፈ/ተከሳሽ አቶ ጌትነት ዳኛው መካከል ባለዉ የገንዘብ ክርክር ጉዳይ በአገው ግ/ቤት ከተማ 02 ቀበሌ በአዋሳኝ በምሥራቅ ግብርና ጽ/ቤት፣ በምዕራብ ወ/ሮ ውዴ ቢያብል፣ በሰሜን ቴሌኮሚኒኬሽን እንዲሁም በደቡብ መንገድ መካከል የሚገኘውን ቤት በአፈ/ተከሳሽ አቶ ጌትነት ዳኛው ስም ተመዝግቦ የሚገኝ ቤት በመነሻ ዋጋ ብር 3,090,526.37 (ሶስት ሚሊዮን ዘጠና ሺህ አምስት መቶ ሃያ ስድስት ብር ከሰላሳ ሰባት ሳንቲም) ይሸጣል፡፡ በመሆኑም  ማስታወቂያ በጋዜጣ ወጥቶ  ለ30 ተከታታይ ቀናት ማለትም ከየካቲት 09/2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ መጋቢት 08/2018 ዓ.ም  ቆይቶ መጋቢት 12/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 6፡00 እንዲሸጥ ፍ/ቤቱ አዝዟል፡፡

ማሳሰቢያ፡- ተጫራቾች ወደ ጨረታው ስትመጡ የጨረታውን መነሻ ዋጋ ¼ ኛውን በሲፒኦ ይዛችሁ እንድትቀርቡ እናሳስባለን፡፡

የባንጃ ወረዳ ፍርድ ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here