የመሬት ሊዝ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
8

የደ/ታቦር ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ በሚደነገገው አዋጅ ቁጥር 721/2004 መሰረት በ2018 በጀት ዓመት 1ኛ ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታ ለመኖሪያ 53 እና ለድርጅት 5 በድምሩ 58 ቦታዎችን በጨረታ ለተጫራቾች ማስተላለፍ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም፡-

  1. ጨረታው በጋዜጣ ከወጣ በኋላ ከጥቅምት 24/2018 እስከ ህዳር 05/2018 ዓ/ም ለ10 ተከታታይ የሥራ ቀን ወጥቶ ይውላል፡፡ ስለዚህ መጫረት የሚፈልግ ማንኛውም አካል  የጨረታ ሰነድ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ቢሮ ቁጥር 07 ድረስ በመምጣት እና በመመዝገብ የማይመለስ ብር 500 /አምስት መቶ ብር/ በመክፈል መግዛት ይችላል፡፡
  2. የጨረታ ሰነድ ማስገቢያ ቀን ከጥቅምት 24/2018 እስከ ህዳር 05/2018 ዓ/ም ድረስ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት በመንግስት የስራ ሰዓት ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 11፡30 ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ግቢ ውስጥ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ቢሮ ቁጥር 07 ይሆናል፡፡
  3. ጨረታው የሚዘጋው ህዳር 05/2018 ዓ/ም በ 11፡00 ይሆናል፡፡
  4. ጨረታው የሚከፈተው ህዳር 06/2018 ዓ/ም 3፡00 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የደ/ታቦር ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ግቢ ውስጥ ነው፡፡
  5. ተጫራቾች የሀሳብና የዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ፣ በባንክ የተረጋገጠ የጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ (ሲፒኦ) ለድርጅት 15 በመቶ እና ለመኖሪያ 20 በመቶ የተከፈለበት  እንዲሁም ኦርጅናል (ዋናውን) ሰነድ የገዙበት ደረሰኝ በፖስታ አሽገው ማስገባት አለባቸው ፡፡
  6. የጨረታ ቦታዎችን በማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ በተለጠፈው ሳይት ኘላን መመልከት በአካል መጎብኘት ይችላሉ፡፡
  7. መሥሪያ ቤቱ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

የደ/ታቦር ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here