የመሬት ሊዝ ጨረታ

0
82

በደ/ጎንደር ዞን ከተማ እና መሰረተ ልማት መምሪያ በሰዴ ሙጃ ወረዳ ከተማ እና መሰረተ ልማት ፅ/ቤት የአዳዳ ከተማ ንዑስ ማዘጋጃ ቤት መሬት ልማት ማናጅመንት ዋና የስራ ሂደት የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ የሚደነግገው አዋጅ 721/2004 መሰረት በ2017 በጀት አመት 1ኛ ዙር ጨረት ለንግድ አገልግሎት የሚውሉ ሶስት ቦታዎች ለቅይጥ አገልግሎት የሚውል አንድ ቦታ ሲሆን ግንባታ የሚገነቡ G+0 የቅይጥ አገልግሎት የሚውል ቦታ ዲዛይን V sheape ሲሆን የንግድ አገልግሎት የሚውለው ቦታ L sheape ለጨረታ የሚቀርቡ መሆናቸውን እየገለፅን፡፡

በአጠቃላይ አራት ቦታዎችን በጨረታ ለተጫራች ማስተላለፍ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም መጫረት የሚፈልግ ሰው ወይም ድርጅት ከ27/08/2017 ዓ.ም እስከ 08/09/2017 ዓ.ም ድረስ ባሉት አስር የስራ ቀናት ውስጥ የጨረታ ሰነድ አዳዳ ከተማ ንዑስ ማዘጋጃ ቤት ቢሮ ድረስ በመምጣት የማይመለስ 400 ብር በመክፈል መግዛት ይቻላል፡፡

  1. የጨረታ ማስገቢያ ቀን ከ27/08/2017 ዓ.ም እስከ 08/09/2017 ዓ.ም ድረስ ባሉት አስር የመንግስት የስራ ቀናት ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 11፡00 ሰዓት በንዑስ ማዘጋጃ ቢሮ ይሆናል፡፡
  2. ጨረታው የሚዘጋው በ08/09/2017 ዓ.ም በ 10 ሰዓት ይሆናል፡፡
  3. ጨረታው የሚከፈተው በ08/09/2017 ዓ.ም በ11 ሰዓት ሁሉም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአዳዳ ከተማ ንዑስ ማዘገጃ ቤት ግቢ ይሆናል፡፡
  4. የጨረታ ቦታዎችን በአካል ለመጎብኘት ከፈለጉ በ08/09/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3 ሰዓት ንዑስ ማዘጋጃ ቤት ድረስ በመገኘት ከጨሬታ ኮሚቴው ጋራ መጎብኘት ይችላሉ ወይም በማስታወቂያ ሰሌዳው ላይ በተለጠፈው ፕላን መመልከት ይችላሉ፡፡
  5. መስሪያ ቤቱ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ በሚል በበኩር ጋዜጣ በአየር ላይ እንዲውልልን ስንል እንጠይቃለን፡፡

                              የአዳዳ ከተማ ንዕስ ማዘጋጃ ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here