የደ/ታቦር ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ በሚደነገገው አዋጅ ቁጥር 721/2004 መሰረት በ2016 በጀት ዓመት 1ኛ ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታ ለመኖሪያ 50 እና ለድርጅት 2 አገልግሎት በድምሩ 52 ቦታዎችን በጨረታ ለተጫራቾች ማስተላለፍ ይፈልጋል፡፡ መጫረት የምትፈልጉ መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
- ጨረታው በአየር ላይ ከሰኔ 3/2016 እስከ ሰኔ 14/2016 ዓ/ም ለ10 ተከታታይ የስራ ቀናት በአየር ላይ ይውላል፡፡መጫረት የሚፈልጉ ግለሰቦች እና ድርጅቶች የጨረታ ሰነድ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ቢሮ ቁጥር 02 ድረስ በመምጣት እና በመመዝገብ የማይመለስ ብር 300.00 /ሶስት መቶ / በመክፈል መግዛት ይቻላል፡፡
- የጨረታ ሰነድ ማስገቢያ ከሰኔ 03 / 2016 እስከ 14/10/2016 ዓ/ም ድረስ ባሉት 10 የስራ ቀናት በመንግስት የስራ ሰዓት ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 11፡00 ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ግቢ ውስጥ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ቢሮ ቁጥር 02 ይሆናል፡፡
- ጨረታው የሚዘጋው ሰኔ 14 /2016 ዓ/ም በ11፡00 ይሆናል፡፡
- ጨረታው የሚከፈተው ሰኔ 15/2016 ዓ/ም በ 3፡30 ሁሉም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በደ/ታቦር ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ግቢ ውስጥ ነው፡፡
- ሁሉም ተጫራቾች በፖስታ አሽገው ማስገባት ያለባቸው ፤የሀሳብና የዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ፣በባንክ የተረጋገጠ የጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ /ሲፒኦ/ ለድርጅት 15በመቶ እና ለመኖሪያ 20በመቶ የተከፈለበት ዋናውን /ኦርጅናል/ ሰነድ የገዙበት ደረሰኝ ናቸው፡፡
- የጨረታ ቦታዎችን በማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ በተለጠፈው ኘላን መመልከት እና በአካል መጎብኘት ይቻላል፡፡
- መስሪያ ቤቱ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡