የእብናት ከተማ አስ/ገ/ጽ/ቤት ለአብናት ከተማ መሰረተ ልማት ጽ/ቤጽ የከተማ ቦታ በሊዝ ስለመያዝ በደነግገው አዋጅ ቁጥር 721/2004 መሰረት በ2016 ዓ.ም በጀት ዓመት 4ኛ ዙር ጨረታ የድርጅት የመሬት 02 G+4 የመሬት ሊዝ በግልፅ ጨረታ አውጥቶ ለተጫራቾች ማስተላለፍ ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም፡-
- የጨረታ ሰነድ መግዣ ቀን በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጅምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት በእብ/ከ/አስ/ገ/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 02 ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 11፡30 ብቻ ይሆናል፡፡
- ቢሮ ቁጥር 02 በመምጣት የማይመለስ 300.00 /ሦስት መቶ ብር/ በመክፈል ሰነዱን መግዛት ይቻላል፡፡
- የጨረታው ሰነድ መሸጫ ጊዜ የሚያልቀው በ10ኛው ቀን 11፡30 ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የመነሻ ዋጋውን በባንክ የተረጋገጠ ክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) በእብናት ከተማ ገ/ጽ/ቤት ስም በማሠራት የተሠራውን (ሲፒኦ) እና ሰነድ የተገዛበትን የ300.00 /የሦስት መቶ ብር/ ደረሰኝ ሁለቱን በአንድ ላይ በማድረግ እብናት ከተማ ገ/ጽ/ቤት ከኦርጅናል የጨረታ ሰነድ ጋር ታሽጎ መቅርብ አለበት፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሀሳቡን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ውስጥ ገቢ አድርጎ ኦርጅናል ሰነዱን የእ/ከ/ገ/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 2 ጨረታው በወጣ በ11ኛው ቀን ማስገባት አለበት፡፡
- ጨረታው ተጫሪቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም በግዥና ፋይናን ቡድን ቢሮ ቁጥር 2 ጨረታው በወጣ በ11ኛዉ ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ታሽጎ 4፡40 ላይ ይከፈታል፡፡ ቀኑ ቅዳሜና እሁድ ወይም የህዝብ በዓል ቀን ከሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
- የቦታዎች የሊዝ መነሻ ዋጋ ለካሬ ለድርጅት 500.00 /አምስት መቶ ብር/ ነው፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ወይም ሲፒኦ በባንክ የተረጋገጠ የገንዘብ ክፍያ አስራ አምስት በመቶ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የተያዘ ገንዘብ አሽናፊ ከተለየ በኋላ የሚመለስ ይሆናል፡፡
- የግንባታ ደረጃ የድርጅት (G+4) ነው፡፡
- መሥሪያ ቤቱ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ውድቅ የማድረግ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- የቦታው አገልግሎት እያዳንዱ ምድብ ከሰንጠረዡ ላይ የተቀመጠው ይሆናል፡፡
- በአጭር ጌዜ ውስጥ ወደ ግንባታ የሚገባና የሚያጠናቅቅ መሆን አለበት፡፡
- ለጨረታ የወጣው የቦታ ብዛት ለድርጅት 02 ነው፡፡
- ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በአካል ጽ/ቤት ድረስ በመምጣት ማግኘት ይችላሉ፡፡