በምዕራብ ጎጃም ዞን ፍ/ሰላም ከተማ አስ/ከ/መ/ል/ጽ/ቤት በ2017 በጀት አመት የ4ኛ ሩብ አመት ለ3ኛ ዙር ለመኖሪያ ፣ለሆቴልና ለገበያ ማዕከል አገልግሎት የሚውሉ የተዘጋጁ ቦታዎችን በሊዝ ጨረታ አወዳድሮ ለማስተላለፍ ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ለመጫረት የሚፈልጉ ማንኛውም ግለሰብ ከግንቦት 18/2017 ዓ.ም ጀምሮ የቦታውን ዝርዝር መረጃ እና የጨረታ ሰነድ ለመኖሪያ ብር 300 /ሶስት መቶ ብር/ ፣ለሆቴልና የገበያ ማዕከል ብር 400 /አራት መቶ ብር/ የማይመለስ በመክፈል እና የጨረታ ሰነድ ማስከበሪያ /ሲፒኦ/ 35 በመቶ በማስያዝ በከተማ አስተዳደሩ ቅጥር ግቢ ቢሮ ቁጥር 76 ድረስ በመምጣት ዘወትር በሥራ ሰዓት ሰነድ መግዛት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
- የጨረታ ሰነድ ማስገቢያ ጊዜ ከ18/09/2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 03/10/2017 ዓ/ም ከቀኑ 11፡00 ብቻ ይሆናል፡፡
- ጨረታው የሚዘጋው በ03/10/2017 ዓ.ም ከቀኑ በ11፡00 ይሆናል፡፡
- ጨረታው የሚከፈተው በ04/10/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 በከተማ አስተዳደሩ ግቢ ሁሉም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይሆናል፡፡
- ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ በስ.ቁ 058 775 17 75 በመደወል መረጃ ማግኘት ይቻላል፡፡
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
የፍ/ሰላም ከተማ አስ/ከ/መ/ል/ጽ/ቤት