የመሬት የሊዝ  ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
78

የእብናት ከተማ አስ/ገ/ጽ/ቤት ለአብናት ከተማ መሰረተ ልማት ጽ/ቤት የከተማ ቦታ በሊዝ ስለመያዝ በደነገገው አዋጅ ቁጥር 721/2004 መሰረት በ2017 ዓ/ም በጀት ዓመት 2ኛ ዙር በጨረታ የድርጅት 01 G+2 የመኖሪያ 04 G+0 አዉጥቶ ለተጫራቾች ማስተላለፍ ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም፡-

  1. የጨረታ ሰነድ መግዣ ቀን በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት በእብ/ከ/አስ/ገ/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 02 ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 11፡30  ብቻ ይሆናል፡፡
  2. ተጫራቾች ቢሮ ቁጥር 02 በመምጣት የማይመለስ ብር 300 /ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል ሰነዱን መግዛት ይቻላል፡፡
  3. የጨረታው ሰነድ መሸጫ ጊዜ የሚያልቀው በ10ኛው ቀን እስከ 11፡30 ብቻ ይሆናል፡፡
  4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የመነሻ ዋጋዉን በባንክ የተረጋገጠ ክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) እብናት ከተማ ገ/ጽ/ቤት ስም በማሰራት የተሰራዉን (ሲፒኦ) እና ሰነድ የተገዛበትን የ300 /የሶስት መቶ ብር/ ደረሰኝ ሁለቱን በአንድ ላይ በማድረግ እብናት ከተማ ገ/ጽ/ቤት ከኦርጅናል የጨረታ ሰነድ ጋር ታሽጎ መቅርብ አለበት፡፡
  5. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሀሳቡን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ውስጥ ገቢ አድርጎ ኦርጅናል ሰነዱን የእ/ከ/ገ/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 2 ጨረታው በወጣ በ11ኛዉ ቀን ማስገባት አለበት፡፡
  6. ጨረታው ተጫራቾች /ህጋዊ ወኪሎቻቸው/ ቢገኙም ባይገኙም በግዥና ፋይናንስ ቡድን ቢሮ ቁጥር 2 ጨረታው በወጣ በ11ኛዉ ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ታሽጎ 4፡40 ላይ ይከፈታል፡፡ ቀኑ ቅዳሜና እሁድ ወይም የህዝብ በዓል ከሆነ በቀጣይ የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
  7. የቦታዎች የሊዝ መነሻ  ዋጋ  ለካሬ ለድርጅት 500 /አምስት መቶ ብር/ ለሌሎቹ  ቦታዎች ግን ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/  ነው፡፡
  8. የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ወይም /ሲፒኦ/ በባንክ የተረጋገጠ የገንዘብ ክፍያ ለድርጅት አስራ አምስት በመቶ ለመኖሪያ ሃያ በመቶ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  9. የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የተያዘ ገንዘብ አሸናፊ ከተለየ በኋላ የሚመለስ ይሆናል፡፡
  10. የግንባታ ደረጃ የድርጅት G+2 ሌሎቹ ደግሞ G+0 ነዉ፡፡
  11. መሥሪያ ቤቱ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ውድቅ የማድረግ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  12. የቦታው አገልግሎት ለእያንዳንዱ ምድብ ከሰንጠረዥ ላይ የተቀመጠው ይሆናል፡፡
  13. በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ግንባታ የሚገባና የሚያጠናቅቅ መሆን አለበት፡፡
  14. ለጨረታ የወጣው የቦታ ብዛት ድርጅት 01 መኖሪያ 04 ነዉ፡፡
  15. ለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በአካል ጽ/ቤት በመምጣት አገልግሎቱን  ማግኘት ይችላሉ፡፡

የእብናት ከተማ አስተዳደር ገ/ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here