የሀሙሲት ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት የከተማ ቦታን በሊዝ ስለማስያዝ በሚደነግገው አዋጅ ቁጥር 721/2004 አንቀጽ 8 ንዑስ አንቀጽ 1 መሰረት በ2018 በጀት አመት 1ኛ ዙር ጨረታ የድርጅት ቦታዎችን በጨረታ አወዳድሮ ለአሸናፊዎች ማስተላለፍ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም፦
- መጫረት የሚፈልጉ ማንኛውም ሰው ወይም ድርጅት ታህሳስ 06/2018 ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 10 የስራ ቀናት ውስጥ የቦታውን ዝርዝር መረጃና የጨረታ ሰነድ ሀሙሲት ከተማና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 1 በመምጣት የማይመለስ ብር 500 (አምስት መቶ ብር) በመክፍል መግዛት ይችላሉ፡፡
- የጨረታ ሰነድ ማስገቢያ ጊዜ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 የስራ ቀናት ከጠዋቱ 2፡30 እስከ ቀኑ 11፡30 ብቻ ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ፡፡
- የጨረታ ሳጥኑ በ10ኛው ቀን በ11፡00 የሚዘጋ ይሆናል፡፡
- ጨረታው የሚከፈተው ሳጥኑ ከተዘጋበት ቀን ቀጥሎ ባለው የሥራ ቀን ከረፋዱ 4፡00 ሁሉም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ሲሆን ቦታው በሀሙሲት ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት ግቢ ይሆናል፡፡
- ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከጽ/ቤቱ የውስጥ ማስታወቂያ በሰሌዳ ላይ መመልከትና በስልክ ቁጥር 058 443 00 62 /04 94 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የሀሙሲት ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት

