የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ

0
90

የጎንደር ከተማ የመጠጥ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽ/ቤት የ2016 በጀት ዓመት ሂሳብ በተፈቀደላቸው ኦዲተሮች ኦዲት ለማስደረግ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ከዚህ በታች የተጠቀሱትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን፡-

  1. ጽ/ቤቱን /ድርጅቱን/ ኦዲት ለማድረግ የሚያስችል የኦዲተርነት የሙያ ፈቃድ ደረጃ ያለው፡፡
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉና የሙያና የንግድ ፈቃዳቸውን ያደሰ፡፡
  3. ተጫራቾች ወቅታዊ ብቃታቸውንና ሙያዊ ስነ-ምግባራቸው በተመለከተ ከፈቃድ ሰጭው አካል ከዋናው ኦዲት መስሪያ ቤት ወይም ከኢትዮጲያ ሒሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ ወይም ከሂሳብ አዋቂዎችና የግል ኦዲተሮች ማሕበር ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. የበጀት ዓመቶች ሂሳብ ኦዲት ለማድረግ በሰጠው ጠቅላላ ዋጋ ላይ የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተመሰከረ ሲፒኦ የጠቅላላ ዋጋውን አንድ በመቶ ማስያዝ የሚችሉ፡፡
  5. ተጫራቾች የሚያከናውኑት ተግባር ከድርጅቱ ጋር ዝርዝር ውል ለመፈራረም ፈቃደኛ የሆኑ፡፡
  6. ተጫራቾች ስለ መልካም ሥራ አፈፃፀማቸው ከአሁን በፊት የሂሳብ ምርመራ /ኦዲት/ ካደረጉባቸው ድርጅቶች የተፃፈላቸውን የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  7. የንግድ ሥራ ፈቃድ የተጨማሪ እሴት ታክስ ሰርተፊኬት /ተመዝጋቢ ከሆነ የግብር ከፋይነት ምስክር ወረቀት /ቲን/ እና ሌሎች ለጨረታው የሚጠቅሙ ማስረጃዎችን የተገናዘበ ፎቶ ኮፒ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  8. የሂሳብ ምርመራ /ኦዲት/ ጎንደር ከተማ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት ቅጥር ግቢ መሆኑን አውቆ የሚሳተፉ፡፡
  9. ተጫራቾች ይህ ጨረታ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት ከ03/06/2017 ዓ.ም እስከ 17/06/2017 ዓ.ም በሥራ ሰዓት በጽ/ቤታችን የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ በማይመለስ ብር 300 /ሶስት መቶ ብር/ በመግዛት ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ጠቅላላ ዋጋቸውን /ታክስን ጨምሮ/ በመሙላት ኦርጅናሉንና ኮፒውን በተለያዩ ፖስታዎች በማሸግ ቢሮ ቁጥር 14 ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  10. ተጫራቾች የበጀት አመቱን ኦዲት ሥራ የኦዲት ሥራው የሚከናወንበትና የሥራ ዝርዝር እና በመጨረሻ የሚያቀርቡት የኦዲት ሪፖርት ይዘት እንዲሁም የሚወሰድባቸውን ጊዜ በተመለከተ የድርጊት መርሃ ግብር /ማስኬጃ ውል/ በማዘጋጀት በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት ይጠበቅባቸዋል፡፡
  11. ጨረታው ለ15 ተከታታይ ቀናት ቆይቶ በ15ኛው ቀን 17/06/2017 ዓ.ም ጠዋቱ 4፡00 ታሽጎ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ቢሮ ቁጥር 14 ይከፈታል፡፡
  12. 15ኛው ቀን በዓል /የእረፍት ቀን/ ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡ በአገር አቀፍ በዓል ምክንያት ካልተዘጋ በስተቀር ዘወትር ቅዳሜ እስከ 6፡00 የሥራ ቀናት ነው፡፡
  13. ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ይሁን በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  14. ለበለጠ መረጃ 058 111 04 59 /058 211 33 16 በመደወል በማነጋገር ይችላሉ፡፡

ፋክስ ቁጥር 058 111 43 72

የጎንደር ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here