የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ

0
95

በሰሜን ጎንደር ዞን በጃናሞራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በሰሩ ለሚገኘው ለጃ/ወ/ት/ጽ/ቤት በ2017 ዓ.ም በመደበኛ የበጀት በዋሰል ቀበሌ ዋሰል 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ለሚያሰራው የአስተዳደር ቢሮ በር በተቋሙ የሚቀርብ ሲሆን የበር መግጠም እና ሌሎች ስራዎችን እና አቅርቦቶች በተቋራጩ የሚሸፈን ሆኖ ግንባታውን በሙሉ ዋጋ ማስገንባት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ መወዳደር ትችላላችሁ።

  1. ደረጃ 7 እና ከዛ በላይ የህንጻ ግንባታ ስራ ተቋራጭ የታደሰና ህጋዊ ንግድ ፍቃድ ፎቶ ኮፒ ማያያዝ አለባቸው ፡፡
  2. ደረጃ 7 እና ከዛ በላይ በህንጻ ግንባታ ስራ ተቋራጭ የታደሰ ሙያ የብቃት ማረጋገጫ ሰርትፍኬት ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
  3. የቲን ተመዝጋቢ የሆኑ፡፡
  4. የተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ተመዝጋቢ ስለመሆናቸው የማረጋገጫ ሰርትፍኬት ማቅረብ አለባቸው፡፡
  5. ተጫራቶች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ 1 እስከ 4 የተጠቀሱትን እና የሚመለከታቸውን ማስረጃወች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  6. የግንባታ አይነትና ዝርዝር መገለጫ /ስፔስፍኬሽን /ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ።
  7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 100 / አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ጃናሞራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 07  ማግኘት ይችላሉ፡፡
  8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና 1በመቶ ከሚሞሉት ጠቅላላ ዋጋ አስበው በሁኔታው ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በመ/ቤቱ ገንዘብ ያዥ በመ/ሂ -1 ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  9. ጨረታው በጋዜጣ ከታተመበት ከ01/07/2017 ዓ/ም እስከ 21/07/2016 ዓ/ም ድረስ ይውላል፡፡
  10. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሀሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ቢሮ ቁጥር 10 ጃ/ወ/ገ/ጽ/ቤት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ቀናት ከ01/07/2017 ዓ.ም እስከ 21/07/2017 ዓ.ም ድረስ ማስገባት ይቻላል፡፡ እንዲሁም ጨረታው ጸንቶ የሚቆየው ለ40 ቀን ይሆናል ፡፡
  11. ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በጃ/ወ/ገ/ጽ/ቤት ውስጥ ቢሮ ቁጥር 10 በቀን 22/07/2017 ዓ/ም 8፡15 ታሽጎ 8፡30 በይፋ ይከፈታል፡፡ ሆኖም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙም የጨረታን ከመክፈት አያስተጓጉለውም፡፡
  12. ጨረታውን የምናወዳድረው በጠቅላላ ድምር /በሎት/ ይሆናል፡፡
  13. የጨረታ ሰነዱ ስርዝ ድልዝ  ካለው ወድቅ ይሆናል ፡፡
  14. ተጫራቾች ከሚሞሉት ሰነድና ፖስታ ላይ የድርጅታቸውን ማህተም ማድረግ አለባቸው፡፡
  15. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ ለሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  16. ተጫራቾ በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ጃናሞራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁ.10 በአካል በመገኘት ወይም በስቁ. 0582940023 በመደወል ማግኘት ይቻላል፡፡

የጃናሞራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

 

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here