የጨረታ ቁጥር ደም/ከ/መ/ል/-01/18
የጨረታ አይነት መደበኛ
የደምበጫ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት የከተማ ቦታን በሊዝ ለመያዝ በሚደነግገው በአዋጅ ቁጥር 721/2004 አንቀጽ 8 ንዑስ አንቀጽ 1 እና 2 ይህን አዋጅ ለማስፈፀም የአብክመ ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ የከተማን ቦታ ሊዝ ስለመያዝ ባወጣው ደንብ ቁጥር 103/2004 በክፍል ሶስት በአንቀጽ 10 ንዑስ አንቀጽ 1 ፊደል ተራ ሀ እስከ ሠ በተዘረዘሩት መሠረት ለመኖሪያ አገልግሎት የተዘጋጁ ቦታዎትን በግልጽ ጨረታ ለተጫራቾች ማስተላለፍ ይፈልጋል፤ በመሆኑም መጫረት የሚፈልጉ ግለሰብ /ድርጅቶች ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት መስከረም 12 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 10 /አስር/ ተከታታይ የሥራ ቀናት የቦታውን ዝርዝር መረጃ እና የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 400 (አራት መቶ ብር) በመክፈል በደምበጫ ከተማ መሰረተ ልማት ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 9 በሥራ ሰዓት መግዛት የሚችሉ ሲሆን በ10ኛው ቀን የጨረታ ሰነድ የሚሸጠው እስከ ቀኑ 11፡00 ብቻ ነው፡፡
- የጨረታ ሰነድ ማስገቢያ ጊዜ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 /አስር/ ተከታታይ የሥራ ቀናት ብቻ ይሆናል፡፡
- የጨረታ ሳጥን የሚታሸገው ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት በ10ኛው ቀን ከቀኑ 11፡00 ነው፡፡
- ቦታውን መጐብኘት የምትፈልጉ ማንኛውም ተጫራች በተቋሙ ማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ በሚገልጽ መርሃ ግብር መሠረት የምናስጐበኝ ይሆናል፡፡
- ጨረታው የሚከፈተው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ በወጣ በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ በ3፡00 በከተማ አስተዳደር አዳራሽ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ይሆናል፤ በ11ኛው ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ ጨረታው በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይሆናል፡፡
- በጨረታዉ የውጭ አገር ዜጎች መጫረት አይችሉም፡፡
- በአንድ አመት ውስጥ ሁለት ጊዜ አሸናፊነቱ ተገልጾ እያለ ቀርቦ ውል ያልፈጸመ በዚህ ጨረታ የማይሳተፍ ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ (ሲፒኦ) የተጫረቱበትን የቦታ ስፋት በቦታው መነሻ ዋጋ በማባዛት የሚገኘውን ውጤት 10 በመቶና ከዚያ በላይ በዝግ አካውንት በማስገባት በባንክ የተመሰከረለት ሰነድ ከዋጋና ሃሳብ ማቅረቢያ ሰነድ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ስለጨረታው ዝርዝር ማብራሪያ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- በጨረታ ለተሸነፉ ተጫራቾች ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የሚመለሰው የጨረታ አሸናፊዉ ከተረጋገጠበት ወይከተገለጸበት ከሚቀጥለዉ ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ስዓት ይሆናል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
- ተጫራቾች ሰነድ በሚገዙበት ጊዜ ማንነታቸዉን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 09 44 12 29 22 ደዉሎ መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የደምበጫ ከተማ አስተዳደር ከተማ እና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት