ዩኒቨርሲቲው ለእርሻ ሜካናይዜሽን ትኩረት ሰጥቷል

0
193

የእርሻ ቴክኖሎጂን ለአካባቢው አርሶ አደሮች
በማስተዋወቅና የዞኑን የምርጥ ዘር እጥረት
ለመፍታት በትኩረት እየሠራ መሆኑን የደባርቅ
ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ።
ዩኒቨርሲቲው የአካባቢውን ፀጋዎች በጥናት
በመለየት በግብርና፣ በትምህርትና በቱሪዝም
ዘርፎች የማሕበረሰቡን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት
ሰጥቶ እየሠራ እንደሚገኝ ነው ያስታወቀው።
በተለይ በግብርናው ዘርፍ የአካባቢውን
የምርጥ ዘር ችግር ለመፍታትና ዘመናዊ የእርሻ
ቴክኖሎጂን ወደ አርሶ አደሩ ለማድረስ እየሠራ
መሆኑን የዩኒቨርሲቲው የጥናትና ምርምር
ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አወቀ ዋሴ ገልፀዋል።
በአካባቢው ያሉ አርሶ አደሮች ዘመናዊ የአስተራርስ
ዘዴዎችንና የሰብል አሰባስብ መንገዶችን
እንዲያውቁ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።
ዳይሬክተሩ እንዳሉት በ2015/2016 የምርት
ዘመን አራት የእርሻ ትራክተር በመግዛት ለአርሶ
አደሩ አስተዋውቀዋል፣ በተመጣጣኝ ዋጋ
በማከራየትና እንዲዋሱ በማድረግ ተጠቃሚ
ሆነዋል። በዚህም ዩኒቨርሲቲው በሚገኝበት
አካባቢ ለሚገኙ አርሶ አደሮች (የሰሜን ጎንደር ዞን)
የምርጥ ዘር ብዜት ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን
አብራርተዋል። ይህም ምርታማነትን ለማሳደግ
እንደሚያስችል ጠቁመዋል።

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here