ጋምቤላ ብሔራዊ ፓርክ

0
157

ጋምቤላ ብሔራዊ ፓርክ በጋምቤላ ክልል ከአገሪቱ ዋና ከተማ አዲስ አበባ በስተምእራብ 850 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ነው የሚገኘው:: ፓርኩ በ1973 ዓ.ም በቀጣናው የሚገኙ የዱር እንስሳትን እና መኖሪያቸውን ለመጠበቅ 50 ሺህ 600 ሄክታር ስፋት ይዞ ነው የተከለለው::

በፓርኩ ክልል የሚገኙት የባሮ እና የጊሎ ወንዞች ለዱር እንስሳቱም ሆነ ለእፅዋቱ አስፈላጊ መሠረት ሆነዋል:: ለዱር እንስሳቱ ከጥም መቁረጫነት ባሻገር ለሳር እና ቅጠላ ቅጠል በሎቹ ልምላሜን ፈጥሮ መልሶ የስጋ በሎቹን ከርስ ይሞላል::

የፓርኩ አበዛኛው ክልል ሳር እና ቁጥቁጦ የለበሰ ነው::

የፓርኩ ቀጣና የኑዌር እና የአኝዋክ ነባር ጐሳዎች መኖሪያ ነው:: በስፋቱም ከሌሎቹ በአገሪቱ ካሉት ሁሉ ቀዳሚ ነው::  ለፓርኩ የሚደረግለት የጥበቃ እና እንክብካቤ ስራዎች  በሚፈለገው መልኩ ውጤታማ አለመሆናቸው ነው የተጠቀሰው:: ለዚህም የደን መመንጠር – ለእርሻ ልማት፤ አደን እና ድንበር ተሻጋሪ ተፈናቃዮች በቀጣናው መስፈራቸው በምክንያትነት ተቀምጧል::

በፓርኩ 69 አጥቢ የዱር እንስሳት መኖራቸውም ተረጋግጧል:: ከነዚህ ውስጥ አንበሳ፣ ዝሆን፣ ጐሽ፣ ቀጭኔ፣ ነብር፣ የሜዳ አህያ ይገኙበታል:: ዓእዋፍን በተለከተም 327 ዝርያዎች እንደሚገኙ ተመዝግበዋል- በፓርኩ:: አብዛኛዎቹ  እንደየወቅቶች ሁኔታ ኮቦታ ቦታ የሚፈልሱ ናቸው::

በወንዞች የተከበበው የፓርኩ ክልል ከየብስ የዱር እንስሳት ባሻገር በዓሳ ሃብትም መገኛነቱም ተጠቃሽ ነው::

በፓርኩ ክልል የሚገኙ የድር እንስሳት እና አእዋፍ ጥበቃ እና እንክብካቤ የተደረጉ ጥረቶች ስኬታማ አለመሆናቸው ነው የተጠቆመው:: ለዘገባችን በመረጃ ምንጭነት ናሽናል ፓርክ ወርልድ ዋይድ እና ዊኪፒዲያን ተጠቅመናል::

(ታምራት ሲሳይ)

በኲር የሚያዝያ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ዕትም

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here