በምሥራቅ ጎጃም ዞን የግንደወይን ከተማ አስተዳደር ከተማ እና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት የመሃል አስፓልት አካፋይ የብረት አጥር ግንባታ በግልጽ ጨረታ በጠቅላላ ሥራ ተቋራጮችን አወዳድሮ ማሠራት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይጋብዛል፡፡
- በዘመኑ የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን/ ያላቸው፡፡
- የግዥው መጠን ከ200,000.00 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ የምስክር ወረቀት ማያያዝ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ለማሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-4 የተጠቀሱትን እና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሠነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የሚገዙ ሥራዎችን ዓይነትና ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፊኬሽን/ ከጨረታ ሰነድ ማግኘት ይቻላል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመልስ 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ በመግዛት የጨረታ ሰነዱን ከመሥሪያ ቤታችን ረዳት ገንዘብ ያዥ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ 100,000.00 /አንድ መቶ ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዛ /ሲ.ፒ.ኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ገቢ ደረሰኝ ማስያዝ አለባቸው፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሀሳቡን በአንድ ወይም በአንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋናና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥና ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ቡድን በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማለትም ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 21 ቀናት ዘወትር በሥራ ሰዓት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ገንዘብ/ጽ/ቤት ኃላፊ ቢሮ ቁጥር 1 በ22 ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ታሽጐ 4፡00 ላይ ይከፈታል፡፡
- መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ሲሆን ተጫራቾች በጨረታው ላወጡት ወጭ መሥሪያ ቤቱ ኃላፊነቱን የማይወስድ መሆኑ ማወቅ ይኖርበታል፡፡
- አሸናፊ ድርጅቱ ያሸነፈባቸውን ማቴሪያሎች ከተማ አስተዳደሩ ድረስ በራሱ ትራንስፓርት ወጭ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
- መስሪያ ቤቱ ጨረታ አሸናፊውን በጥቅል ዋጋ ይለያል፡፡
- ተጫራቾች ጨረታው ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ አቤቱታ /ቅሬታ/ ካላቸው በተከታታይ 5 የሥራ ቀናት ቅሬታ ማቅረብ የሚችሉ ሲሆን ከ5 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውጭ የመጣ ቅሬታ ጽ/ቤቱ የማይቀበል መሆኑን እንገልፃለን፡፡
- መሥሪያ ቤቱ ከአሸናፊ ድርጅቱ ያሸነፋቸውን ሥራዎች ሃያ በመቶ ከውል በፊት የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ሥራዎች በባለሙያ እየተረጋገጡ ርክክብ የሚፈፀም ይሆናል፡፡
- የጨረታ መክፈቻ ቀኑ በዓል፣ ቅዳሜ እና እሁድ ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን የሚከፈት መሆኑን ጽ/ቤቱ ይገልፃል፡፡
- አሸናፊ ድርጅቱ አሸናፊነቱ ከተገለጸለት ከ5 የሥራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናቶች ውስጥ መጥቶ ውል በመያዝ የውል ማስከበሪያ አስር በመቶ ማስያዝ ይኖርበታል፡፡
- ከአሸናፊው ድርጅት ሃያ በመቶ የቅድመ ግብር የሚቆረጥ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
- ግዥ ፈፃሚው አካል ግዥውን ለመገምገም፣ ለማፅደቅ፣ አቤቱታ ቢነሳ ለማስተናገድ እና አሸናፊ ድርጅቱ ጋር ውል እስገሚገባ ድረስ የመጫረቻ ሰነዱ ጸንቶ የሚቆየበት ለ60 ቀን ይሆናል፡፡
- ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ግዥና ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ቡድን በአካል በመገኘት ወይም በስልክ በቁጥር 058 861 26 15 በመደወል ዝርዝር መረጃውን ማግኘት ይቻላል፡፡