ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
96

በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የወገራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ለወረዳው ሴክተር መሥሪያ ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ ሎት 1 አላቂ የጽሕፈት መሣሪያዎች ፣ሎት 2 አላቂ የጽዳት እቃዎች ፣ሎት 3 የኤልትሮኒክስ እቃዎች ፣ሎት 4 የመኪና ጎማ ፣ሎት 5 የኤክልትሮኒክ እቃዎች ጥገና እና ሎት 6 የመኪና እቃ መለዋወጫ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተለውን መስፈርት የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይጋብዛል፡፡ የመወዳደሪያ  መስፈርቶችም፡-

  1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆኑ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. የንግድ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
  4. የግዥ መጠን ከ200,000.00 /ሁለት መቶ ሽህ ብር/ እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  5. ተጫራቾች በጨረታ ለማሸነፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-4 ተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  6. የሚገዙ እቃዎችን አይነትና ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ ብቻ በመክፈል ዘወትር በሥራ ሰዓት ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 02  ማግኘት ይችላሉ፡፡
  8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለሚወዳደሩበት የእቃውን ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡
  9. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ (አንድ ወጥ በሆኑ) ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋናና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በወ/ወ/ገንዘብ ጽ/ቤት በግ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 03 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት እስከ 22/04/2017 ዓ/ም 3፡30 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  10. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በወ/ወ/ገንዘብ ጽ/ቤት በግ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 03 በቀን 22/04/2017 ዓ/ም በ4፡00 ይከፈታል፡፡
  11. መ/ቤቱ ስለ ጨረታ የተሻለ ዘዴ /አማራጭ / ከአገኘ ጨረታውን በከፊል ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ነው፡፡
  12. የጨረታው አሸናፊ የሚለየው በሎት ወይም በተናጠል በየሎት ምድባቸው የሚለይ ይሆናል፡፡
  13. ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 09 16 23 50 60 /09 48 47 78 83 /09 23 77 63 77 ወይም ቢሮ ቁጥር 3 በአካል በመገኘት ማብራሪያ ማግኘት የሚቻል መሆኑን እናሳስባለን፡፡

የወገራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here