ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
89

የምዕራብ ጎንደር ዞን /ከፍ/ፍ/ቤት ለ2017 በጀት አመት አገልግሎት የሚውሉ በሥሩ ያሉትን 1. መተማ ወ/ፍ/ቤት 2. ምዕራብ አርማጭሆ ወ/ፍ/ቤት 3. አዳኝ አገር ጫቆ ወ/ፍ/ቤት 4. ቋራ/ወ/ፍ/ቤት አገልግሎት የሚሰጡ ሎት 1 ስቴሽነሪ ሎት 2 ቋሚ ዕቃ ሎካል፣ ሎት 3 የጽዳት እቃ፣ ሎት 4 ልዩ ልዩ፣ ሎት 5 ኤሌክትሮኒክስ ሎት 6 ህትመት እና ሎት 7 የመኪና እቃ  በሎት ተዘርዝሮ ያቀረበ ሲሆን፡፡ የተዘረዘሩትን ሎቶች በግልጽ ጨረታ  አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በዚህ መሰረት መወዳደር የሚፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መሰፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል፡፡

  1. የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን/ ያላቸው፡፡
  4. የግዥ መጠኑ ከ200,000.00 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ በላይ ከሆነ ተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸዉን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  5. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር ከ1-4 የተጠቀሱት እና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከማጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  6. የሚገዙ እቃዎችን አይነትና ዝርዝር መገለጫ /ስፔስፊኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ00 /ሃምሳ ብር/ በመክፈል ከግዥ ክፍል ቢሮ ቁጥር 32 ማግኘት ይቻላል፡፡
  8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ወይም /ቢድ ቦንድ/ ለሚወዳደሩበት የእቃውን ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና /በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡
  9. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋናና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በምዕ/ጎ/ዞን/ከፍ/ፍ/ቤት በግ/ፋ/ን/አስ/ሂደት/ቢሮ ቁጥር 32 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት ከ14/04/2017 ዓ/ም እስከ 28/04/2017 ዓ/ም ድረስ ከቀኑ 11፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ በቀን 28/04/2017 ዓ.ም ከቀኑ 12፡00 የጨረታ ሳጥኑ ይታሸጋል፡፡
  10. ጨረታው ተጫራቾች ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ምዕ/ጎን/ዞን/ከፍተኛ ፍርድ ቤት ግ/ፋ/ን/አስ/ሂደት በቀን 30/04/017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡30 ውስጥ በግዥ ክፍል ቢሮ ቁጥር 32 ይከፈታል፡፡
  11. መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  12. ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በአካል ቢሮ ቁጥር 32 ድረስ በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 831 07 58 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
  13. ከተጫራቾች መካከል አሸናፊው ንብረቱን የሚያስረክበውና ውል የሚወስደው በምዕ/ጎ/ዞን/ከፍ/ፍ/ቤት መሆኑን እንገልጻለን፡፡

የምዕራብ ጎንደር ዞን /ከፍ//ቤት

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here