በደ/ጎንደር ዞን የሰዴ ሙጃ ወረዳ ገ/ኢ/ት/ጽ/ቤት ግን/አስ ቡድን ለ2017 በጀት አመት ለመንገድ ትራንስፖርት ጽ/ቤት አገልግሎት የሚውል የዶዘር ኪራይ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ ከዚህ በታች የተዘረዘረውን መስፈርት ማሟላት የምትችሉ፡-
- በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የግብር ከፋይ /ቲን/ ያላቸው፡፡
- ተጫራቾች የሞሉት ዋጋ ከ200,000.00 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ መሆኑን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ ከ1-3 የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ሙሉ አድራሻቸውን በድርጅቱ ስም የተዘጋጀ ማህተም መምታት አለባቸው፡፡
- የሚገዙ እቃዎችን አይነትና ዝርዝር መግለጫ ስፔስፊኬሽን ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለሚወዳደሩበት የእቃውን ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ /በመሂ1 ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ጨረታውን ካሸነፉ በኃላ አስር በመቶ የውል ማስከበሪያ በጥሬ ገንዘብ (በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ) ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ለ15 ተከታታይ ቀን በአየር ላይ ይውላል፡፡
- ጨረታው በ16ኛው ቀን በ3፡00 ይታሸግና በዚሁ ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ግ/ን/አስ ቢሮ ቁጥር 2 በዚሁ ቀን 3፡30 ይከፈታል፡፡ ሆኖም ተጫራቾች በራሳቸው ምርጫ ጨረታው በሚከፈትበት ወቅት ባይገኙ የጨረታውን መከፈት የማያስተጓጉሉ አይሆኑም ከመሆኑም በተጨማሪ በጨረታ ሃደቱ ለተላለፉ ውሳኔዎች ተገዥ ይሆናሉ፡፡
- ከጨረታ ሰነዱ ላይ ሥርዝ ድልዝ መሆን የለበትም፡፡
- ጨረታው የሚከፈትበት የበዓል ቀን ከሆነ በቀጣይ የሥራ ቀን ይከፈታል፡፡
- በማስታወቂያ ያልተገለጹ ካሉ በግዥ መመሪያው መሰረት ተፈጻሚ ይሆናሉ፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
- ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ግ/ን/አስ ቢሮ ቁጥር 2 ድረስ በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 09 18 28 07 69 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
የሰዴ ሙጃ ወረዳ ገንዘብና ኢኮነሚ ት/ጽ/ቤት