ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
107

በደ/ጎንደር ዞን አ/ዘመን ከተማ የሚገኘው ርብ ኃላ/የተወሠነ የኅብረት ስራ ማኅበራት ገንዘብ ቁጠባና ብድር ዩኒዬን ቀበሌ 04 በመደበኛ በጀት ለጽ/ቤት አገልግሎት የሚውል ባለቢዝመንት ሦስተኛ ፎቅ (B+G+3 ፎቅ) ለማሰራት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ተጫራቾች  ለብረት አቅራቢዎች በግልጽ ጨረታ የግዥ ዘዴ አወዳድሮ በመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈረቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችል በመሆኑን  ይጋብዛል፡፡

  1. አቅራቢዎች ህጋዊና በዘመኑ የታደሠ የንግድ /የሥራ/ ፈቃድ እንዲሁም ከመንግስት የሚጠበቅባቸውን የዘመኑን ግብር የከፈሉና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር የተቀበሉ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  2. የወጣው ጨረታ 200,000.00 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ እና በላይ ዋጋ እንደሚሆን ሲገመት የተጨማሪም የእሴት ታክስ /ቫት/ ከፋይነት የተመዘገበ መሆኑን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ ይኖርበቸዋል፡፡
  3. የጨረታ ማስከበሪያ ሁለት በመቶ በባንክ በተረጋገጠ ክፍያ ትዕዛዝ ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ ይኖረባቸዋል፡፡
  4. ተጫራቾች የሚያቀረቡት የመጫረቻ ሰነድ በአማረኛ ቋንቋ መዘጋጀት ይኖርበታል፡፡
  5. ተጫራቾች በሚሞሉበት የመወዳደሪያ ሃሳብ  ስማቸውን ፣ፊርማቸው እና ሙሉ አድራሻቸውን ማስፈር ይኖረባቸዋል፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱ በአ/ዘመን ከተማ 500.00 /አምስት መቶ ብር/ በመክፈል ለሃያ አምስት ተከታታይ ቀናት የመጫረቻ ሠነዱን ዋናው ጽ/ቤት ድረስ በመምጣት በአካል /ህጋዊ ወኪላቸው በኩል መግዛት ይቻላል፡፡
  7. የጨረታ መዝጊያው ጊዜ ከተጠናቀቀ በኋላ ተጫራቾች ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ ላይ ለውጥ ወይም ማሻሻያ ማድረግና ከጨረታው ራሳቸውን ማግለል አይችሉም፡፡
  8. የብረት አይነት ፣ብዛትና ዝርዝር መግለጫ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
  9. የመጫረቻ ሰነዱን ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን ለ25 ተከታታይ ቀናት ከቀኑ 11፡30 ድረስ ማስገባት ይችላሉ፡፡
  10. የመጫረቻ ሰነዱ በ26 ተኛው ቀን ከረፋዱ 4፡00 ደረስ ማስገባትና በ4፡00 ተዘግቶ በዕለቱ 4፡30 ተጫራቾች /ህጋዊ ወኪሎች/ በተገኙበት/ ባይገኙም/ ይከፈታል፡፡
  11. ማንኛውም ተጫራች የጨረታው ሰነዱ በአንድ በጥንቃቂ በታሸገ ፖስታ በተዘጋጀ የጨረታ ሣጥን የጨረታ ማስከበሪያውን ከኦሪጅናል ሰነዶ ፖስታ ውሥጥ በማደረግ  መቅረብ አለባቸው፡፡
  12. ዩኒዬኑ ጨረታውን በከፊል ወይም በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  13. የብረት አቀራረብ ሁኔታ በተመለከተ ተጫራቾች መመሪያ ይመልከቱ፡፡
  14. አሸናፊው ተጫራች የውል ማስከበሪያ አስር በመቶ ማስያዝ ይኖረባቸዋል፡፡
  15. ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 058 444 00 61 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

ርብ ኃላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ስራ ማኅበራት ገንዘብ ቁጠባና ብድር ዩኒዬን

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here