ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
102

የቢቡኝ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት በብ/የሚ/የግ/ግክ/ ቡድን በ2017 በጀት አመት ለጽ/ቤቱ አገልግሎት የሚውል የማንጎ ዘር በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይጋብዛል፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸዉና የብቃት ማረጋገጫ ስርተፊኬት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸዉ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ እና የግብር ከፋይ መለያ (ቲን) ተመዝጋቢ የሆኑ፡፡
  3. የግዥ መጠን ከ200,000.00 (ሁለት መቶ ሽህ ብር/ እና ከዚያ በላይ ከሆነ ተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋገጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. የማንጎ ዘሩ 50 (ሃምሳ) ኩንታል ሁኖ በዛፉ ላይ በጣም የበሰለ ወደ ቢጫነት የተቀየረ ከበሽታና ተባይ ነጻ የሆነ ያልተላጠ እና ግብዓቱ ሲቀርብ ከኳራንታይን የጥራት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችል፡፡
  5. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተ.ቁ 1-4 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸዉን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ የአሰሪው መ/ቤት እና የተጫራቹ ሙሉ ስም አድራሻ ፊርማ ማህተም በማስቀመጥ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸዉ ጋር አያይዘዉ ማቅረብ አለባቸዉ፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ለመግዛት00 /ሰላሳ ብር/ የማይመለስ በመክፈል ከቢ/ወ/ገ/ኢ/ል/ፅ/ቤትደ/ሂ/ደ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 12 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት የእቃዉን ጠቅላላ ዋጋ ሁለት በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ አለባቸዉ፡፡
  8. ማንኛዉም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ቢ/ወ/ግ/ፅ/ቤት/በብ/የሚ/የግ/ግ/ክ ቡድን ቢሮ ቁጥር 06 በተዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት ከ12/05/2017 ዓ.ም እስከ 30/05/2017 ዓ.ም 10፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ በዚሁ ቀን 10፡00 ላይ ይታሸጋል፡፡
  9. ጨረታዉን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ግብ/ፅ/ቤት/በብ/የሚ/የግ/ግ/ክ ቡድን በቢሮ 06 በ01/06/2017 ዓ.ም በ 3፡00 ይከፈታል፡፡
  10. አሸናፊው ድርጅት አሸናፊነቱ በተገለፀበት ከ5 የሥራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የአሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ አስር በመቶ በማስያዝ ውል መያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  11. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ሲሆን ሃያ በመቶ የመጨመርም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
  12. መ/ቤቱ ጨረታውን በሚከፍትበት ቀን ብሄራዊ በዓል እና እሁድ ቅዳሜ  ከሆነ በቀጣይ የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
  13. ግብዓቱ የሚቀርበው በሙሉ ወይን ዉሃ ችግኝ ጣቢያ ሲሆን በሙያተኛ ተረጋግጦ ገቢ ይደረጋል፡፡
  14. ሰለጨረታዉ ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 06 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 254 06 04 ወይም 09 13 79 98 34 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡

የቢቡኝ ረዳ ግብርና ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here