ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
87

የቢቡኝ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት የግዥና ን/አስ/ቡድን ለቢቡኝ ወረዳ መስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ጽ/ቤት በገና መምቻ ቀበሌ አረፋ ወንዝ የካናል ጥገና እና ማራዘም ሥራ በ2017 በጀት ዓመት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማስገንባት ይፈልጋል፡፡ ሰለዚህ ለመጫረት የሚፈልጉ ሁሉ ከዚህ በታች የተጠቀሱትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባችኃል፡፡

  1. በአዲሱ አዋጅ መሠረት የታደሰ ንግድ ሥራ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን/ ያላቸው፡፡
  3. የግዥ መጠኑ 200,000.00 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ እና ከዚያ በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋገጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. የታደሰ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬትና በመስኖ አውታር ሥራ የሰራና የመልካም ሥራ አፈፃፀም ማቅረብ የሚችል፡፡
  5. በውሀ ሥራ ኮንስትራከሽን (WWC) ደረጃ 7 እና ከዚያ በላይ የሙያ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  6. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-5 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃ ኦርጅናልና ፎቶ ኮፒ ለየብቻዉ በማሸግና በእያንዳንዱ ፖስታ ላይ የአሰሪዉ መሥሪያ ቤትና የተጫራቹን ሙሉ ስምና አድራሻ ፊርማና ማህተም በማስቀመጥ ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  7. አሸናፊ ተጫራች ማሸነፉ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ከ5 የሥራ ቀናት በኋላ ባሉት በ5 ተከታታይ ቀናት ዉስጥ የጨረታ አሸናፊዉ የዉል ማስከበሪያ ጠቅላላ ዋጋውን አስር በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና /በጥሬ ገንዘብ/ በመሂ 1 ማስያዝ አለባቸዉ፡፡
  8. የመስኖ ካናል ጥገና እና ማራዘም የሥራ ዝርዝር ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  9. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን00 /አምስት መቶ ብር/ የማይመለስ ብር በመክፈል ከፋይናንስ ቡድን ቢሮ ቁጥር 12 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  10. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ ለሚወዳደሩበት ብር የግንባታውን ጠቅላላ ዋጋ00 /ሀያ አምስት ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና በጥሬ ገንዘብ በመሂ 1 ማስያዝ አለባቸው፡፡
  11. ተጫራቾች የጨረታ ሃሳባቸዉን ዋናውንና ቅጁን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በቢ/ወ/ገንዘብ/ጽ/ቤት በግዥ/ን/አ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 01 በተዘጋጀው የጨረታ ማስገቢያ ሳጥን ዘወትር በሥራ ስዓት ከ26/05/2017 እስከ 16/06/2017 ዓ.ም 11፡30 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  12. ጨረታዉ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሉቻቸው ቢገኙም ባይገኙም በግዥ/ን/አሰ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 01 በ22 ኛዉ ቀን በ17/06/2017 ዓ.ም 3፡00 ይታሸጋል በዚሁ ቀን 3፡30 ይከፈታል፡፡
  13. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ከአገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ሲሆን ሃያ በመቶ የመጨመር የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
  14. በነጠላም ሆነ በጠቅላላ ዋጋ ላይ ሥርዝ ድልዝ መኖር የለበትም በአጠቃላይ በ2014 በጀት ዓመት የወጣውን የተሻሻለውን የግንባታ የግዥ መመሪያ ተግባራዊ የምናደርግ ይሆናል፡፡
  15. መ/ቤቱ ጨረታዉ በሚከፈትበት ቀን ብሄራዊ በዓል ቀን ከሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓትና ቀን ይከፈታል፡፡
  16. ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 01 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 254 00 47 /49 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡

የቢቡኝ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here