በደ/ጎንደር ዞን አ/ዘመን ከተማ የሚገኘው ርብ ኃላ/የተወሠነ የኅብረት ስራ ማኅበራት ገንዘብ ቁጠባና ብድር ዩኒዬን ቀበሌ 04 በመደበኛ በጀት ለጽ/ቤት አገልግሎት የሚውል ባለቢዝመንት ሦስተኛ ፎቅ (B+G+3 ፎቅ) ለማሰራት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ተጫራቾች ለሚቀርቡ ለብረት አቅራቢዎች በወስን ጨረታ የግዥ ዘዴ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈረቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ በመሆኑን ይጋብዛል፡፡
- አቅራቢዎች ህጋዊና በዘመኑ የታደሠ የንግድ /የስራ/ ፈቃድና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር የተቀበሉ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የወጣው ጨረታ ብር 200,000 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ እና በላይ ዋጋ እንደሚሆን ሲገመት የተጨማሪም የእሴት ታክስ /ቫት/ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆኑን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ ይኖርበቸዋል፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ ሁለት በመቶ በባንክ በተረጋገጠ ክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ ይኖረባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የሚያቀረቡት የመጫረቻ ሰነድ በአማረኛ ቋንቋ መዘጋጀት ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች በሚሞሉበት የመወዳደሪያ ሃሳብ ስማቸውን፤ ፊርማቸው እና ሙሉ አድራሻቸውን ማስፈር ይኖረባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱ በአ/ዘመን ከተማ ብር 500 /አምስት መቶ ብር/ በመክፈል ለ15 ተከታታይ ቀናት የመጫረቻ ሠነዱን ዋናው ጽ/ቤት ድረስ በመምጣት በአካል /ህጋዊ ወኪላቸው በኩል መግዛት ይችላሉ፡፡
- የጨረታ መዝጊያው ጊዜ ከተጠናቀቀ በኋላ ተጫራቾች ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ ላይ ለውጥ ወይም ማሻሻያ ማድረግና ከጨረታው ራሳቸውን ማግለል አይችሉም፡፡
- የብረት አይነት፤ ብዛትና ዝርዝር መግለጫ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
- የመጫረቻ ሰነዱን ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን 15 ተከታታይ ቀናት ከቀኑ 11፡30 ድረስ ማስገባት ይችላሉ፡፡
- የመጫረቻ ሰነዱ በ16 ኛው ቀን ከረፋዱ 4፡00 ማስገባትና በ4፡00 ተዘግቶ በዕለቱ 4፡30 ተጫራቾች /ህጋዊ ወኪሎች/ በተገኙበት/ ባይገኙም/ ይከፈታል፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታው ሰነዱ በአንድ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በተዘጋጀ የጨረታ ሣጥን የጨረታ ማስከበሪያውን ከኦሪጅናል ሰነዱ ፖስታ ውሥጥ በማድረግ መቅረብ አለባቸው፡፡
- ዩኒዬኑ ጨረታውን በከፊል ወይም በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- የብረት አቀራረብ ሁኔታ በተመለከተ ተጫራቾች መመሪያ ይመልከቱ፡፡
- አሸናፊው ተጫራች የውል ማስከበሪያ አስር በመቶ ማስያዝ ይኖረባቸዋል፡፡
- ግልጽ ያልሆኑ ጉዳዬችን በስልክ ቁጥር 058 444 00 61 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
ርብ ኃላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ስራ ማኅበራት ገንዘብ ቁጠባና ብድር ዩኒዬን