ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
99

በደቡብ ጎንደር ዞን የእስቴ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በወረዳዉ ለሚገኙ ሴክተር መ/ቤቶች ምድብ 1 ኤሌክትሮኒክስ፣ ምድብ 2 የዉሃ ግንባታ ማቴሪያል፣ ምድብ 3 የመንገድ ጥገናና የማሽን ኪራይ፣ ምድብ 4 የስፖርት ትጥቅ በመደበኛ በጀት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት እና ማሰራት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም የሚከተሉትን መሰፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይጋብዛል፡፡

  1. የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸው፡፡
  3. የግዥው መጠን ብር 200,000 /ሁለት መቶ ሽህ ብር/ እና ከዚያ በላይ ከሆነ የተጨማሪ ዕሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትን እና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  5. የሚሰሩ ሥራዎችን /የሚገዙ እቃዎችን/ አይነት እና ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፊኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኝት ይችላሉ፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ ለእያንዳንዱ ሰነድ በመክፍል ከግ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 1 ማግኝት ይቻላል፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ማሰከበሪያ ዋስትና ለኤሌክትሮኒክስ ግዥ 40000 /አርባ ሽህ ብር/፣ ለዉሃግንባታ ማቴሪያል ግዥ 20000  /ሃያ ሽህ ብር/፣ ለመንገድ ጥገና ስራዉ 50000 /ሃምሳ ሽህ ብር/ እና ለስፖርት ትጥቅ ግዥ 5000 /አምስት ሽህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በጥሪ ገንዘብ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  8. ተጫራቾች የዉል ማሰከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ ለሚወዳደሩበት ጠቅላላ ዋጋ አስር በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒ.ኦ/ ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  9. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥ ክፍል ቢሮ ቁጥር 1 ጨረታው በጋዜጣ በወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው ቀን 3፡30 ታሸጎ 4፡00 ይከፈታል። ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙም ጨረታውን ከመክፈት አያስተጓጎልም፡፡ የመክፈቻ ቀኑ በዓል ቢሆን በሚቀጥለዉ የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
  10. በሚቀርበው የመጫረቻ ሰነድ ላይ በነጠላ እና በጠቅላላ ዋጋ ላይ ልዩነት ቢፈጠር በነጠላ ዋጋዉ የሚወሰድ ይሆናል፡፡ የመጫረቻ ሰነዱ ስርዝ ድልዝ ካለበት ተጫራቾች ከጨረታ ውጭ ይሆናሉ፡፡
  11. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  12. ጨረታው በእያንዳንዱ ምድብ በጥቅል ድምር ስለሚወዳደር ሁሉንም እቃዎች መሙላት ይጠበቅበታል፡፡
  13. ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 1 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 09 20 67 19 18 /09 18 30 30 12 በመደውል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡

የእስቴ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here