ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
110

የማእከላዊ ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በ2017 በጀት ዓመት ለተለያዩ የሥራ ሂደቶችና ለምድብ ችሎቱ  አገልግሎት የሚሰጡ እቃዎችን ለመግዛት  ሎት 01 የጽህፈት መሳሪያዎች፣ ሎት 2  የጽዳት እቃዎች፣  ሎት 03 የመኪና መለዋወጫ እቃዎች፣  ሎት 04 የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች እና ሎት 05 የፈርኒቸር እቃዎች በሎት ለመግዛት መስፈርቱን አሟልቶዉ ከሚገኙ አቅራቢ ድርጅቶች አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ሥለሆነም፡-

  1. ተጫራቾች በዘርፉ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸዉና የታደሰ፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ እንዲሁም የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ሰርተፊኬት አያይዘዉ ከጨረታ ሰነዱ ጋር የሚያቀርቡ ሲሆን፣ ግዥዉ ከ200,000 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ እና ከዚያ በላይ ለሚፈጸሙ ግዥዎች እና ለኤሌክትሮኒክስ ነክ እቃዎች የቫት ተመዝጋቢ መሆን አለባቸዉ፡፡ የጨረታ ሰነዱን ለእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ ብር 30 /ሰላሳ ብር/ ብቻ በመክፈል ከማ/ጎን/ከፍ/ፍ/ቤት የግ/ፋ/ንብ/አስ/ ቡድን ቢሮ ቁጥር 5 በመቅረብ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
  2. ጨረታዉ የካቲት 24 ቀን 2017 ዓ.ም እስከ መጋቢት 8 ቀን 2017 ዓ.ም በጋዜጣ ተለጥፎ ቆይቶ መጋቢት 9 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ላይ የጨረታ ሳጥኑ ታሽጎ በታሸገበት ቀን ከቀኑ 8፡15 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ጨረታዉ ማ/ጎ/ዞን/ከ/ፍ/ቤት ቢሮ ቁጥር 5 በግልጽ ይከፈታል፡፡ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በቀኑና በሰዓቱ ካልተገኙ ጨረታዉን ከመክፈት አያግድም፡፡
  3. የዕቃ ዓይነት እና ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፊኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ሙሉዉን መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በሎት ድምር ከሞሉት ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ ከሆነ ከመ/ቤታችን የግዥ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ቡድን ቢሮ ቁጥር 5 ከገንዘብ ያዥ በመ/ሂ1 ደረሰኝ አስቆርጦ ከሚወዳደርበት ሰነድ ጋር የደረሠኝ ኮፒ በማሸግ ማስገባት አለባቸዉ፡፡
  5. ማንኛዉም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወጥ በሆነ ዋና ሠነድ በጥንቃቄ  በታሸገ  ፖስታ  በተራ ቁጥር 2 በተገለጸዉ ቦታ መጋቢት 9 ቀን 2017 ዓ.ም እስከ ቀኑ 8፡00 ድረስ ሰነዱን በተዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን ዉስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  6. ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ የእቃዉን መጓጓዣና እንዲሁም ማንኛዉንም የመንግስት ታክስን ያካተተ ሆኖ መቅረብ አለበት፡፡
  7. መሥሪያ ቤቱ ጨረታዉን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡ ዉድድሩ በሎት ድምር ወይም በነጠላ ዋጋ የማወዳደር መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
  8. ጥያቄ ወይም ማብራሪያ ካለዎት ግዥና ፍይናንስ ንብረት አስተዳደር ቡድን ቢሮ ቁጥር 5 በአካል በመቅረብ ወይም  በስልክ ቁጥር 058 111 44 40  ደዉለዉ መጠየቅ ይችላሉ፡፡

የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ከፍ/ፍ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here