ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
75

በምሥራቅ ጎጃም ዞን በሞጣ ከተማ አስተዳደር ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ለሞጣ ጤና አጠ/ጣቢያ አገልግሎት የሚውሉ ሎት 1 የጽዳት እቃዎች፣ ሎት 2 የጽህፈት መሳሪያ እና ሎት 3 ሌሎች ቋሚና አላቂ እቃዎች ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ ሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች እንድትወዳደሩ ተጋብዛችኋል፡፡

  1. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  2. ተወዳዳሪዎች በዘመኑ የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  3. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን/ ያላቸው፡፡
  4. ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-3 ድረስ የተዘረዘሩትን የሚመለከታቸውን ማስረጃ ፎቶ ኮፒ በማድረግ ከጨረታ ሠነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  5. ተወዳዳሪዎች የጨረታ ሃሳባቸውን በአንድ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በሞጣ ጤና አጠ/ጣቢያ ግ/ፋ/ን/አስ/ደ/የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 7 ማስታወቂያው በጋዜጣ በወጣበት በመጀመሪያ ቀን አንስቶ ተከታታይ 15 ቀናት ቆይቶ የሚውል ሲሆን የጨረታ ሰነዱን በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ዘወትር በሥራ ሰዓት አስከ 16ኛው ቀን 4፡00 ማስገባት ይጠበቅባቸዋል፡፡
  6. ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ግ/ፋ/አስ/ደ/የስራሂደት ቢሮ ቁጥር 7 በ16ኛው ቀን 4፡15 ላይ ይከፈታል ቀኑ ቅዳሜና እሁድ ወይም የህዝብ በዓል ከሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
  7. የጨረታ ሠነዱን ቢሮ ቁጥር 7 ብር 50 (ሀምሳ ብር) የማይመለስ በመክፈል መውሠድ ይችላሉ፡፡
  8. የሚገዙ እቃዎች አይነትና ዝርዝር መግለጫ ሰፔስፊኬሽን ከጨረታ ሠነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  9. ስለጨረታው ዝርዝር ሁኔታ ለመጠየቅ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 058 661 00 02 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
  10. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  11. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የጠቅላላ ዋጋውን ሁለት በመቶ በባንክ በተረጋገጠ ከፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
  12. መ/ቤቱ የሚገዙትን እቃዎች ሃያ በመቶ የመጨመር የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  13. የሚገዙ እቃዎችን አሸናፊው ተቋሙ ድረስ አጓጉዞ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡
  14. አሸናፊ የሚለየው በሎቱ ወይም በጠቅላላ ድምር ይሆናል፡፡
  15. የግዥ መጠኑ ከ200,000 ሁለት መቶ ሺህ ብር/ በላይ ከሆነ ተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ማስያዝ አለባቸው፡፡

የሞጣ ከተማ ጤና ጥበቃ ጣቢያ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here