ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
92

በደቡብ ጎንደር አስተዳደር ዞን የስማዳ ወረዳ ገንዘብ/ጽ/ቤት ግ/ን/አስ/ድን በ2017 ዓ/ም በመደበኛ በጀት እና በስፖርት ምክር ቤት በጀት ለስማዳ ወረዳ መንገድና ትራንስፖርት ጽ/ቤት ሥር ከወገዳ ቄስውሃ ፈንቶሜዳ እና ከወገዳ ሰኞ ገበያ አስፋሜዳ ለሚያሰራዉ መንገድ የጠጠር ማልበስ ሥራ ለማስራት ሎት 1 ሮሎ እና ግሬደር ማሽን እና ሎት 2 የስፖርት እቃና አልባሳት በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት መግዛት ይፈልጋል፡፡ ለማሽኑ ነዳጅን ጨምሮ ማንኛውንም ወጭ በጨረታ አሸናፊ የሚሸፈን ይሆናል፡፡ በመሆኑም፡- ተጫራቾች ማሟላት የሚፈለግባቸው መስፈርቶች

  1. ህጋዊ /ወቅታዊ/ የታደሰ የዘርፉ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉና ቲን ካርድ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. ተጫራቾች የሞሉት ዋጋ ብር 200,000 /ሁለት መቶ ሽህ ብር/ እና በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
  4. ተጫራቾች የጨረታ ሠነዳቸውንና ሌሎች መረጃዎቻቸውን በፖስታ በማሸግ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ስማዳ ወረዳ ግ/ን/አስደ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 26 ለሥራው በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
  5. ጨረታው በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ታሽጎ 4፡30 ይከፈታል፡፡
  6. ተጫራቾች ከሚያቀርቡት የመወዳደሪያ ሀሣብ ስማቸውን ፊርማቸውን ማህተማቸዉንና ሙሉ አድራሻቸውን ማስፈር አለባቸው፡፡
  7. የጨረታው ጊዜ ከተጠናቀቀ በኋላ ተጫራቾች ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሀሣብ ላይ ለውጥ /ማሻሻያ/ ማድረግና ከጨረታው እራሣቸውን ማግለል አይችለም ሥርዝ ድል ፍፁም የተከለከለ ነዉ፡፡
  8. ጨረታውን ለማዛባት የሚሞክሩ ተጫራቾች ከጨረታ ውጭ እንደሚሆኑና ለወደፊቱም በመንግስት የግዥ ጨረታ እንዳይሳተፉ የሚደረጉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
  9. ተጫራቾች ለሥራው የተዘጋጀውን ሠነድ የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ ብቻ በመክፈል ዘወትር በሥራ ሰዓት ስ/ወ/ገ/ያዥ ቢሮ ቁጥር 12 መግዛት ይችላሉ፡፡
  10. ተጫራቾች ከሚያቀርቡት አጠቃላይ ዋጋ አንድ በመቶ የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ ለዋና ገንዘብ ያዥ ማስያዝና ያስያዙበትን ኮፒ ፖስታ ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
  11. ተጫራቾች የባለቤትነት የሚገልጽ ሊብሬ ኮፒዉን በዉል ጊዜ ማያያዝ አለባቸዉ፡፡
  12. ጨረታው የሚከፈትበት ቀን የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይሆናል፡፡
  13. ተጫራቾች ጨረታውን ካሸነፉ በኋላ አስር በመቶ የውል ማስከበሪያ በጥሬ ገንዘብ በባንክ በተረጋገጠ /ሲፒኦ/ ማቅረብና ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  14. ለበለጠ ማብራሪያ በሥልክ ቁጥር 058 667 01 67 ደውሎ ወይም ግ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 27 በአካል ጠይቆ መረዳት ይቻላል፡፡

የስማዳ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here