ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
82

የምስ/ጐጃም ዞን ክፍ/ፍ/ቤት ግዥ ፋ/ን/አስ/ቡድን ለመ/ቤታችን እገልግሎት የሚውል 1. የመኪና አቃዎች 2.የፎቶ ኮፒ እና የኘሪንተር መለዋወጫ አቃዎች 3 ሁለገብ የጥገና እቃዎች በበኩር ጋዜጣ በግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ መጫረት ይችላሉ፡፡

  1. የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው
  2. የግብር ከሩይ ምዝገባ ሰርተፍኬት /ቲን/ ያላቸው፣
  3. ከብር 200,000/ ሁለት መቶ ሺህ ብር/ እና ከዚያ በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. ተጫራቾች በጨረታ በመሣተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትን እና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር አያይዞ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፣
  5. የሚገዙት እቃዎችን አይነት ዝርዝር መግለጫ የያዘ / አስፔስፊኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ።
  6. ከላይ የተጠቀሱትን አቃዎች ሰነድ ከምስ/ጐጃም ዞን ከፍ/ፍ/ቤት ከግዥ/ፋይ/ንብ/አስ/ድን ከዋና ገንዘብ ያዥ ቢሮ በመምጣት ብር 50/ ሃምሣ ብር/ በመግዛት መውሰድ ይቻላሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለሚወዳደሩበት የአቃዎች ጠቅላላ ዋጋ 1 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡
  8. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በጥንቃቄ በመሙላት በታሸገ ፖስታ ከግዥ ፋ/ቢሮ ቁጥር 103 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት አለባቸው፡
  9. ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በበኩር ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምር ስተከታታይ 15 ቀናት በአየር ላይ ውሎ በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ተዘግቶ ወዲያውኑ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም ይከፈታል።
  10. አሸናፊው ከጠቅላላ ዋጋ 1 በመቶ /ሲፒኦ/ ወይም በጥሬ ገንዘብ የውል ማስከበሪያ ማስያዝ ይጠበቅበታል ::
  11. አሸናፊው እቃዎችን ምስ/ጐጃም ዞን ከፍ/ፍ/ቤት ንብረት ክፍስ ቢሮ ድረስ በማምጣት ማስረከብ ይጠበቅበታል፡፡
  12. 20 በመቶ መቀነስም ሆነ መጨመር የሚችል መሆኑን እየገለጽን ነገር ግን መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  13. የጨረታ መክፈቻው ቀን የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይከፈታል፡፡ በዚህ ያልተጠቀሱ በግዥ መመሪያው የተቀመጡ የተጫራቾች መመሪያ ተግባራዊ ይደረጋሉ፡፡
  14. ዝርዝር መረጃ ለማግኘት ቢሮ ቁጥር 103 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 0587715550 መጠየቅ ይቻላል፡፡

ምስራቅ ጎጃም ዞን ከፍ/ፍ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here