የቡሬ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ቡሬ በ2017 በጀት ዓመት ዓመታዊ ውል በመያዝ ለተኝቶ ህክምና ታካሚዎች እና ካፌ አገልግሎት የሚዉል ሎት 1 የበሰለ ምግብ አቅርቦት በሆቴሎችና ካፍቴሪያ ዘርፍ ፈቃድ ላላቸው ግለሰቦች በግልጽ ጨረታ አውጥቶ ማስቀረብ እና የሆስፒታሉን ካፍቴሪያ በብር 10,000 /አስር ሺህ ብር/ ብቻ ማከራየት ይፈልጋል፡፡ በካፌው የሚቀርቡ አገልግሎቶች፡- 1. የምግብ አይነት የተለያዩ ምግብ አይነቶችን ፣2. የተለያዩ አይነት ትኩስ መጠጦች የጀበና ቡናን ጨምሮ ፣3. የተለያዩ አይነት ቀዝቃዛ መጠጦችን ከአልኮል ወጭ እና መቀመጫ ወንበር ፣ 4. ጠረጴዛ ማቅረብ የሚችል እና 5 የሻይ ማሽን ፍራጅ ቴሌቪዥን እና ሌሎች ቁሳቁሶችን አሸናፊ ተጫራች ያቀርባል፡፡
- በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸዉ፡፡
- የግብር ክፍያ መለያ ቁጥር /ቲን/ ያላቸዉ፡፡
- የግዥ መጠኑ ከብር 200,000 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸዉን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸዉ ጋር አያይዘዉ በታሸገ ፖስታ ማቅረብ አለባቸዉ፡፡ ከላይ ከ1-3 የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ያላቀረቡ ተጫራቾች ከጨረታው ውጭ ይሆናሉ፡፡
- የሚቀርቡ የምግብ እና የመጠጥ አይነትና ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፊኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ ብቻ በመክፈል ከግ/ፋ/ንብ/አስ/ሂደት ቢሮ ቁጥር 63 መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለሚወዳደሩበት ብር ጠቅላላ ዋጋ 2 በመቶ በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይችላሉ፡፡
- ማንኛዉም ተጫራቾች የጨረታ ሀሳቡን በአንድ ወይም በአንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋናና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በቡሬ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ቡሬ ከግ/ፋ/ን/አስ/ደ/የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 63 በተዘጋጀዉ ሳጥን ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት እስከ 16ኛው ቀን 2፡59 ድረስ ማስገባት ይችላሉ፡፡
- ጨረታዉ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉን በተገኙበት በቡሬ የመ/ ደ/ሆስፒታል ውስጥ የጨረታ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በግ/ፋ/ን/አስ/ደጋፊ የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 63 በ16ኛው ቀን 3፡00 ታሽጎ 3፡30 በይፋ ይከፈታል፡፡ ቀኑ በዓል ወይም እሁድ ቅዳሜ ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ታሽጎ በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
- የጨረታው አሸናፊ ከተለየ በኋላ በሚቀጥሉት 5 የሥራ ቀናት በ5 ተከታይ ቀናት ውስጥ የውል ማስከበሪያ ካሸነፈው ጠቅላላ ዋጋ 10 በመቶ በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ በማስያዝ ውል መያዝ ይኖርበታል፡፡
- ከተጨማሪ እሴት ታክስ በፊት ብር 10,000 /አስር ሺህ ብር/ እና በላይ ከተፈጸመ ዊዝ ሆልዲንግ ታክስ ሁለት በመቶ ይቀነሳል፡፡
- ስለጨረታዉ ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በግ/ፋ/ንብ/አስ/ደ/የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 63 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 774 05 76 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- የጨረታው አሸናፊ መሆን የሚችለው በተጫረተበት ዘርፍ በጥቅል ዋጋቸው ዝቅተኛ ዋጋ የሞላውን በመምረጥ ነው፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡ ሆኖም ጨረታዉ በመሰረዙ ምክንያት ተጫራቾች ላወጡት ዋጋ ሆስፒታሉ ተጠያቂ አይሆንም፡፡
ማሳሰቢያ፡-
- ተጫራቾች የካፌዉን እና የተኝቶ ታካሚዎችን ምግብ ተለይቶ መሙላት አለባቸው፡፡
- የካፌዉ ወርሀዊ ኪራይ ብር 10,000 /አስር ሺህ/ ሆኖ የሚቀርቡ ምግብ እና መጠጦች በጨረታ ሰነዱ ላይ የተገለፁትን መሆን አለበት፡፡
- መብራት እና ዉሃ በሆስፒታሉ ካለ የሚቀርብ ሆኖ በሆስፒታሉ በማይኖርበት ጊዜ አሸናፊዉ ገዝቶ የሚጠቀም ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች ለካፍተሪያዉ ከተዘረዘሩት የምግብና የመጠጥ ዓይነቶች በተጨማሪ ከአልኮል ዉጭ በተመጣጣኝ ዋጋ ማቅረብ ይችላሉ፡፡
የቡሬ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል